🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 28/2018(ኢዜአ)፦ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በዚህ ሳምንት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በመረቁበት ወቅት የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በአዲሱ ዓመት ከሚጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ለፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እንደገለጹት የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የግንባታ ማብሰሪያ መርሃ ግብር በዚህ ሳምንት ይከናወናል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ላለፉት በርካታ አስርት ዓመታት ሲጠቀምበት መቆየቱን አስታውሰዋል።
የአየር መንገዱ አገልግሎት በሰፋበት ወቅት አውሮፕላን ማረፊያው የአቅሙ መጨረሻ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።

በዚህም ምክንያት የአየር መንገዱን አገልግሎት በብቃት የሚሸከመው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ይፋ መሆኑን ተናግረዋል።
10 ቢሊየን ዶላር ወጪ የሚደረግበት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ የሚሸጋገርበት የግንባታ ማብሰሪያ መርሃ ግብር በዚህ ሳምንት እንደሚከናወን ጠቁመዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026