የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል-አቶ አህመድ ሺዴ

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል ሲሉየገንዘብ ሚኒስትርአህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡

‎ከሰባት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የነበረው የማክሮ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ስብራት ውስጥ የነበረ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ የእዳ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የገበያ አለመረጋጋት ከለውጡ በፊት የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚው ዋና ስብራቶች ሆነው ቆይተዋል ብለዋል።

‎መንግሥት እነዚህን ስብራቶች ለመለወጥ በወሰዳቸው የለውጥ ተግባራት አሁን ላይ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ ሲሉም ተናግረዋል።

ይህም ለውጥ ኢትዮጵያ በአፍሪካ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ሃገራት መካከል እንድትሆን እንዳስቻላት ገልጸዋል።

የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል ያሉት ሚኒስትሩ ለውጡ ካመጣቸው ውጤቶች መካከል የመንግስት ገቢን ለማሳደግ የሚያግዙ ጠንካራ፣ አዳዲስ እና ቀልጣፋ ስትራቴጂዎች እንዲነደፉ አድርጓል ብለዋል።

ከለውጡ በኋላ የመንግስት ገቢ የውጭ ፍሰትን ጨምሮ በአምስት እጥፍ አድጓል፤የመንግስት የታክስ ገቢ በ400 % ጨምሯል ነው ያሉት።

የመንግስት ጠቅላላ ገቢ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት ዛሬ ላይ 446 በመቶ ጨምሯል ብለዋል። ከውጭ ሃብት ፍሰትም ባለፉት ሰባት ዓመታት በአጠቃላይ 25 ቢሊየን ዶላር ማግኘት ያስቻለ ውጤት የተመዘገበበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በድህነት ተኮር ዘርፎች የዋለው በጀት በ2010 ከነበረበት በአራት እጥፍ ያደገ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ የበጀት ጉድለትን በተመለከተ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 2.5 በመቶ በ2017 ወደ 0.9 በመቶ መቀነስ ተችሏል ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026