🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል ሲሉየገንዘብ ሚኒስትርአህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡
ከሰባት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የነበረው የማክሮ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ስብራት ውስጥ የነበረ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ የእዳ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የገበያ አለመረጋጋት ከለውጡ በፊት የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚው ዋና ስብራቶች ሆነው ቆይተዋል ብለዋል።
መንግሥት እነዚህን ስብራቶች ለመለወጥ በወሰዳቸው የለውጥ ተግባራት አሁን ላይ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ ሲሉም ተናግረዋል።
ይህም ለውጥ ኢትዮጵያ በአፍሪካ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ሃገራት መካከል እንድትሆን እንዳስቻላት ገልጸዋል።
የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል ያሉት ሚኒስትሩ ለውጡ ካመጣቸው ውጤቶች መካከል የመንግስት ገቢን ለማሳደግ የሚያግዙ ጠንካራ፣ አዳዲስ እና ቀልጣፋ ስትራቴጂዎች እንዲነደፉ አድርጓል ብለዋል።
ከለውጡ በኋላ የመንግስት ገቢ የውጭ ፍሰትን ጨምሮ በአምስት እጥፍ አድጓል፤የመንግስት የታክስ ገቢ በ400 % ጨምሯል ነው ያሉት።
የመንግስት ጠቅላላ ገቢ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት ዛሬ ላይ 446 በመቶ ጨምሯል ብለዋል። ከውጭ ሃብት ፍሰትም ባለፉት ሰባት ዓመታት በአጠቃላይ 25 ቢሊየን ዶላር ማግኘት ያስቻለ ውጤት የተመዘገበበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።
በድህነት ተኮር ዘርፎች የዋለው በጀት በ2010 ከነበረበት በአራት እጥፍ ያደገ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ የበጀት ጉድለትን በተመለከተ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 2.5 በመቶ በ2017 ወደ 0.9 በመቶ መቀነስ ተችሏል ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025