🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል ሲሉየገንዘብ ሚኒስትርአህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡
ከሰባት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የነበረው የማክሮ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ስብራት ውስጥ የነበረ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ የእዳ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የገበያ አለመረጋጋት ከለውጡ በፊት የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚው ዋና ስብራቶች ሆነው ቆይተዋል ብለዋል።
መንግሥት እነዚህን ስብራቶች ለመለወጥ በወሰዳቸው የለውጥ ተግባራት አሁን ላይ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ ሲሉም ተናግረዋል።
ይህም ለውጥ ኢትዮጵያ በአፍሪካ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ሃገራት መካከል እንድትሆን እንዳስቻላት ገልጸዋል።
የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል ያሉት ሚኒስትሩ ለውጡ ካመጣቸው ውጤቶች መካከል የመንግስት ገቢን ለማሳደግ የሚያግዙ ጠንካራ፣ አዳዲስ እና ቀልጣፋ ስትራቴጂዎች እንዲነደፉ አድርጓል ብለዋል።
ከለውጡ በኋላ የመንግስት ገቢ የውጭ ፍሰትን ጨምሮ በአምስት እጥፍ አድጓል፤የመንግስት የታክስ ገቢ በ400 % ጨምሯል ነው ያሉት።
የመንግስት ጠቅላላ ገቢ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት ዛሬ ላይ 446 በመቶ ጨምሯል ብለዋል። ከውጭ ሃብት ፍሰትም ባለፉት ሰባት ዓመታት በአጠቃላይ 25 ቢሊየን ዶላር ማግኘት ያስቻለ ውጤት የተመዘገበበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።
በድህነት ተኮር ዘርፎች የዋለው በጀት በ2010 ከነበረበት በአራት እጥፍ ያደገ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ የበጀት ጉድለትን በተመለከተ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 2.5 በመቶ በ2017 ወደ 0.9 በመቶ መቀነስ ተችሏል ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026