የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የልማት ውጥኖቻችን ፍሬ እያፈሩ እንደሚገኙ ምስክር የሚሆኑ ስራዎች እየተሰሩ ነው - አቶ አደም ፋራህ

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የልማት ውጥኖቻችን ፍሬ እያፈሩ እንደሚገኙ ምስክር የሚሆኑ ስራዎች እየተሰሩ ነው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ፡፡

የብልጽግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት አፈፃፀም ግምገማ በክልሉ ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

አቶ አደም ፋራህ ከግምገማ መድረኩ ጎን ለጎን የሰላም አምባሳደር በሆነችውና በፍጥነት በማደግ ላይ ባለችው ሆሳዕና ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸውን አስታውቀዋል።


በከተማዋ ዘመናዊነትን ከባህላዊ ትሩፋቶች ጋር በማጣመር ዘመናዊ የእግረኛ መንገድ፣ የአውቶብስ መጠበቂያ፣ ስማርት የኤሌክትሪክ ፖሎች የተገጠሙለትና አካል ጉዳተኞችን ያማከለ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኮሪደር ልማት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በከተማው የተገነባው የአቢዮ ኤርሳሞ ስታዲየምን የጎበኙ ሲሆን፥ ስታዲየሙ ወጣቶችን በስነምግባር አንጾ ለማሳደግና የስፖርቱን ዘርፍ ለመደገፍ እንዲሁም ፓርቲው በማህበራዊ ዘርፍ እየሰራ ለሚገኘው ስራ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።

ሀዲይ ነፈራ (የሀዲያ ደጃፍ) ተብሎ የተሰየመውን የታላቁ የሀዲያ ህዝብ ወግ፣ ባህልና የአኗኗር ዘይቤን አጣምሮ የያዘውን የባህል መንደር መጎብኘታቸውን ገልጸው፥ በተለያዩ አካባቢዎች በቱሪዝም ዘርፍ እየታዩ ላሉ መነቃቃቶች ሁነኛ ማሳያ እንደሚሆን አመልክተዋል።


በተጨማሪም በከተማዋ እጅግ ባጠረ ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃውን የርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት የተመለከቱ ሲሆን፥ ይህም በክልሉ ለሥራ ምቹ ተቋማትን ለመገንባት ለተያዘው ግብ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ነው ያሉት፡፡

በክልሉ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች የብልጽግና ፓርቲ የልማት ውጥኖች በአግባቡ ተግባራዊ ተደርገው ፍሬ እያፈሩ እንደሚገኙ ምስክር የሚሆን ነው ማለታቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡

በአመራሩና በህብረተሰቡ የጋራ ጥረት እየተገኙ የሚገኙ ውጤቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቶ አደም ፋራህ መልዕክት ማስተላለፋቸውንም በዘገባው ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025