🔇Unmute
ነቀምቴ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት ከምሥራቅ ወለጋ ዞን 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ደረጄ ነጋሳ ገለጹ።

በበጀት ዓመቱ በቡና ከለማው 47 ሺህ ሔክታር ከ73 ሺህ ቶን በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከዚህም 292 ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን እና እስካሁን 30 ቶን ምርት መቅረቡን ነው ለኢዜአ ያረጋገጡት።

የቡና ጥራትን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ከቡና ግብይት ጋር የተያያዙ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን የመከላከል ሥራ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።
አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርትም በኅብረት ሥራ ዩኒየኖች በኩል ለገበያ እንዲያቀርብ እየተደረገ ስለመሆኑም ተናግረዋል።
የቡና ምርት ለመሰብሰብ የቡና አምራቾችን እና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026