የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ከምሥራቅ ወለጋ ዞን 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀረበ

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት ከምሥራቅ ወለጋ ዞን 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ደረጄ ነጋሳ ገለጹ።


በበጀት ዓመቱ በቡና ከለማው 47 ሺህ ሔክታር ከ73 ሺህ ቶን በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከዚህም 292 ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን እና እስካሁን 30 ቶን ምርት መቅረቡን ነው ለኢዜአ ያረጋገጡት።


የቡና ጥራትን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ከቡና ግብይት ጋር የተያያዙ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን የመከላከል ሥራ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርትም በኅብረት ሥራ ዩኒየኖች በኩል ለገበያ እንዲያቀርብ እየተደረገ ስለመሆኑም ተናግረዋል።

የቡና ምርት ለመሰብሰብ የቡና አምራቾችን እና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026