የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ከምሥራቅ ወለጋ ዞን 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀረበ

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት ከምሥራቅ ወለጋ ዞን 30 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ደረጄ ነጋሳ ገለጹ።


በበጀት ዓመቱ በቡና ከለማው 47 ሺህ ሔክታር ከ73 ሺህ ቶን በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከዚህም 292 ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን እና እስካሁን 30 ቶን ምርት መቅረቡን ነው ለኢዜአ ያረጋገጡት።


የቡና ጥራትን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ከቡና ግብይት ጋር የተያያዙ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን የመከላከል ሥራ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል።

አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርትም በኅብረት ሥራ ዩኒየኖች በኩል ለገበያ እንዲያቀርብ እየተደረገ ስለመሆኑም ተናግረዋል።

የቡና ምርት ለመሰብሰብ የቡና አምራቾችን እና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026