🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ አስደናቂ ኅብረ-ባህል፣ ነባርና አዳዲስ የመስኅብ ስፍራዎችን የታደለች ውብ ሀገር ናት ሲሉ የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ተናገሩ።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስቡ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ መዳረሻዎች ያሏት ሀገር ናት፡፡

የኢትዮጵያን እምቅ ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና የተፈጥሮ መስኅብ እንዲሁም ውብ የሆኑ አዳዲስ የመስኅብ ስፍራዎችን መጎብኘታቸውን ገልጸዋል።
ለጤና ተስማሚ የሆነና ሁሉንም ሥርዓተ-ምኅዳር የሚያካትት የተለየ የአየር ጸባይ የታደለች ውብ ሀገር መሆኗንም ጠቅሰዋል፡፡

አዲስ አበባ ከዚህ በፊት ከተመለከቷቸው በርካታ የዓለም ከተሞች በልዩነት ውብ ሆና እንዳገኟት ከቤልጂየም የመጡት ጎብኚ ቴር ጊለር ተናግረዋል።
ከተማዋ ፅዱ፣ ነፋሻማ፣ አረንጓዴ እና ለጎብኚዎች ታሪክን የሚያስረዱ በርካታ መዳረሻዎች መያዟ ቀልባቸውን በእጅጉ እንደገዛውም አንስተዋል።

ብሔራዊ ሙዝዬምንና እንጦጦ ፓርክን ጨምሮ የተለያዩ መዳረሻዎችና ፓርኮችን መጎብኘታቸውን ገልጸው፤ በዚህም እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

ከጀርመን የመጡት ሉካስ ኩፐንሃገል በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ከተመለከቷቸው የቱሪዝም መዳረሻዎች በተጨማሪም በሀገሪቱ ኅብረ-ብሔራዊ ዕሴቶች መደነቃቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ መስኅቦች የደመቀች ሀገር መሆኗንም ዐይቻለሁ ብለዋል።

በኢትዮጵያ ነባር መዳረሻዎችን መልሶ የማልማትና አዳዲስ አስደናቂ የመስኅብ ቦታዎች መገንባታቸው የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምር ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ የታላቁ ኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅቶች ማኅበር ምክትል ፕሬዚዳንት እንቁ ሙሉጌታ ናቸው።
ኢትዮጵያ የብዝኃ-ባህል፣ ታሪክ እና የበርካታ መዳረሻዎች መገኛ መሆኗ በዘርፉ ለተሰማሩ ባለድርሻ አካላት ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም ጠቁመዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፤ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች ለቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከማበርከታቸው በላይ የሀገርን ገጽታ የቀየሩና የግሉ ዘርፍ እንዲበረታታ በር የከፈቱ ድንቅ ሥራዎች ናቸው ብለዋል፡፡
መዳረሻዎቹ የጎብኚ ቁጥር እንዲጨምር እና የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ በማድረግ ከፍተኛ የሆነ ምጣኔ ሃብታዊ፣ ማኅበራዊና፣ ዲፕሎማሲያዊ ጠቀሜታ እያስገኙ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026