🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመኸር ወቅቱ ከለማው ሰብል እስካሁን ድረስ 138 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን በክልሉ 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ማልማት ተችሏል።
በመኸር ወቅቱ ከለማው ሰብል ከ187 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱንም አስታውቀዋል።

እስካሁንም በ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ሰብል የምርት ብክነትን በቀነሰ መልኩ በቴክኖሎጂና በሰው ጉልበት ታግዞ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከተሰበሰበው ሰብልም 138 ሚሊዮን ኩንታል የገብስ፣ የስንዴ፣ የጤፍ፣የበቆሎ፤ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።
በምርት አሰባሰቡ 76 ኮምባይነሮችና በ517 ሁለገብ የሰብል መውቂያና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖች ጥቅም ላይ መዋላቸውን ነው የገለጹት።
በምስራቅ ጎጃም ዞን የደብረኤልያስ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አባትሁን ስራው እንዳሉት፤ በሦስት ሄክታር ተኩል መሬት ላይ ያለሙትን የስንዴ፣ የበቆሎና የጤፍ ስብል በኮምባይነርና በሰው ጉልበት ታግዘው ሰብስበዋል።

የስንዴና የጤፍ ሰብላቸውን ወቅተው የተሻለ ምርት ወደጎተራ እንዳስገቡ ጠቅሰው፣ የበቆሎ ሰብላቸውን ደግሞ በማሽን ታግዘው እየፈለፈሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሦስት ሄክታር መሬት ላይ ያለሙትን የስንዴ፣ የቢራ ገብስና የባቄላ ሰብል መሰብሰባቸውን የገለጹት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የእስቴ ወረዳ አርሶ አደር ብርሃን ይመር ናቸው።
ሰብሉን በሰው ጉልበት በመውቃት ወደጎተራ እያስገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአማራ ክልል በ2016/2017 የመኸር ወቅት በክልሉ ከለማው 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት 170 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025