🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመኸር ወቅቱ ከለማው ሰብል እስካሁን ድረስ 138 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን በክልሉ 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ማልማት ተችሏል።
በመኸር ወቅቱ ከለማው ሰብል ከ187 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱንም አስታውቀዋል።

እስካሁንም በ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ሰብል የምርት ብክነትን በቀነሰ መልኩ በቴክኖሎጂና በሰው ጉልበት ታግዞ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከተሰበሰበው ሰብልም 138 ሚሊዮን ኩንታል የገብስ፣ የስንዴ፣ የጤፍ፣የበቆሎ፤ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።
በምርት አሰባሰቡ 76 ኮምባይነሮችና በ517 ሁለገብ የሰብል መውቂያና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖች ጥቅም ላይ መዋላቸውን ነው የገለጹት።
በምስራቅ ጎጃም ዞን የደብረኤልያስ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አባትሁን ስራው እንዳሉት፤ በሦስት ሄክታር ተኩል መሬት ላይ ያለሙትን የስንዴ፣ የበቆሎና የጤፍ ስብል በኮምባይነርና በሰው ጉልበት ታግዘው ሰብስበዋል።

የስንዴና የጤፍ ሰብላቸውን ወቅተው የተሻለ ምርት ወደጎተራ እንዳስገቡ ጠቅሰው፣ የበቆሎ ሰብላቸውን ደግሞ በማሽን ታግዘው እየፈለፈሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሦስት ሄክታር መሬት ላይ ያለሙትን የስንዴ፣ የቢራ ገብስና የባቄላ ሰብል መሰብሰባቸውን የገለጹት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የእስቴ ወረዳ አርሶ አደር ብርሃን ይመር ናቸው።
ሰብሉን በሰው ጉልበት በመውቃት ወደጎተራ እያስገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአማራ ክልል በ2016/2017 የመኸር ወቅት በክልሉ ከለማው 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት 170 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026