🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመኸር ወቅቱ ከለማው ሰብል እስካሁን ድረስ 138 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን በክልሉ 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ማልማት ተችሏል።
በመኸር ወቅቱ ከለማው ሰብል ከ187 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱንም አስታውቀዋል።

እስካሁንም በ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ሰብል የምርት ብክነትን በቀነሰ መልኩ በቴክኖሎጂና በሰው ጉልበት ታግዞ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከተሰበሰበው ሰብልም 138 ሚሊዮን ኩንታል የገብስ፣ የስንዴ፣ የጤፍ፣የበቆሎ፤ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።
በምርት አሰባሰቡ 76 ኮምባይነሮችና በ517 ሁለገብ የሰብል መውቂያና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖች ጥቅም ላይ መዋላቸውን ነው የገለጹት።
በምስራቅ ጎጃም ዞን የደብረኤልያስ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አባትሁን ስራው እንዳሉት፤ በሦስት ሄክታር ተኩል መሬት ላይ ያለሙትን የስንዴ፣ የበቆሎና የጤፍ ስብል በኮምባይነርና በሰው ጉልበት ታግዘው ሰብስበዋል።

የስንዴና የጤፍ ሰብላቸውን ወቅተው የተሻለ ምርት ወደጎተራ እንዳስገቡ ጠቅሰው፣ የበቆሎ ሰብላቸውን ደግሞ በማሽን ታግዘው እየፈለፈሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሦስት ሄክታር መሬት ላይ ያለሙትን የስንዴ፣ የቢራ ገብስና የባቄላ ሰብል መሰብሰባቸውን የገለጹት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የእስቴ ወረዳ አርሶ አደር ብርሃን ይመር ናቸው።
ሰብሉን በሰው ጉልበት በመውቃት ወደጎተራ እያስገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአማራ ክልል በ2016/2017 የመኸር ወቅት በክልሉ ከለማው 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት 170 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026