🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የቴክኖሎጂ ፈጠራ በወሳኝ ጥቂት የሕክምና ዘርፎች የሚታየውን የሰው ሃይል እጥረት ለመሙላት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ገለፁ።
የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አድርገዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው በጉብኝታቸው በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን መመልከታቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በጤናው ዘርፍ ለተግባራዊ አገልግሎት የሚውሉ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል።

የጤና እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ባለሙያዎች በቅንጅት መስራት የሚቻልበት ሁኔታ መኖሩ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል።
ይህም በሀገሪቱ የሰው ኃይል እጥረት ባለባቸው የሕክምና ዘርፎች ላይ የሚታየውን ክፍተት ለመሙላት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ሰፊ ዓለም አቀፍ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ዶክተር ከሰተብርሃን ጠቁመዋል፡፡
በቦርድ አባልነት የሚያገለግሉበት ሴፒ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ወረርሽኝ ሊያስከትሉ የሚችሉ ቫይረሶችን ቀድሞ በመለየት በ100 ቀናት ውስጥ ክትባቶችን ለማምረት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ተቋሙ በአፍሪካ ውስጥ አብረውት ሊሰሩ የሚችሉ ማዕከሎችን በመፈለግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጉብኝታቸው በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በሴፒ መካከል ጠንካራ የሥራ ግንኙነት ለመፍጠር ዕድል እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ይህም የኢትዮጵያ የጤና ምርምር ተቋማት ሴፒ የሚያዘጋጃቸውን የኤ አይ ኢንጂኖች (AI Engines) በስፋት መጠቀም የሚችሉበትን መንገድ እንደሚያመቻች አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025