የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢንስቲትዩት የቴክኖሎጂ ፈጠራ በወሳኝ ጥቂት የሕክምና ዘርፎች የሚታየውን የሰው ኃይል እጥረት ለመሙላት ከፍተኛ ሚና አለው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የቴክኖሎጂ ፈጠራ በወሳኝ ጥቂት የሕክምና ዘርፎች የሚታየውን የሰው ሃይል እጥረት ለመሙላት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ገለፁ።

የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አድርገዋል።


ዋና ሥራ አስፈጻሚው በጉብኝታቸው በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን መመልከታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በጤናው ዘርፍ ለተግባራዊ አገልግሎት የሚውሉ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል።


የጤና እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ባለሙያዎች በቅንጅት መስራት የሚቻልበት ሁኔታ መኖሩ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል።

ይህም በሀገሪቱ የሰው ኃይል እጥረት ባለባቸው የሕክምና ዘርፎች ላይ የሚታየውን ክፍተት ለመሙላት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ሰፊ ዓለም አቀፍ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ዶክተር ከሰተብርሃን ጠቁመዋል፡፡

በቦርድ አባልነት የሚያገለግሉበት ሴፒ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ወረርሽኝ ሊያስከትሉ የሚችሉ ቫይረሶችን ቀድሞ በመለየት በ100 ቀናት ውስጥ ክትባቶችን ለማምረት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ተቋሙ በአፍሪካ ውስጥ አብረውት ሊሰሩ የሚችሉ ማዕከሎችን በመፈለግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጉብኝታቸው በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በሴፒ መካከል ጠንካራ የሥራ ግንኙነት ለመፍጠር ዕድል እንደሚኖረው ገልጸዋል።

ይህም የኢትዮጵያ የጤና ምርምር ተቋማት ሴፒ የሚያዘጋጃቸውን የኤ አይ ኢንጂኖች (AI Engines) በስፋት መጠቀም የሚችሉበትን መንገድ እንደሚያመቻች አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026