የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና ማያ ከተማ አስተዳደር ከ11ሺህ በላይ ከሆኑ የኢኮኖሚ ድርጅቶች መረጃ ይሰበሰባል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረማያ ፤ጥር 14/2018 (ኢዜአ) ፡-በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና ማያ ከተማ አስተዳደር ከ11ሺህ በላይ ከሆኑ የኢኮኖሚ ድርጅቶች መረጃ የመሰብሰብ ስራ ይከናወናል።

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የሐረር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለሚያከናውኑ የመስኩ ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ነው።

በአገልግሎቱ የሐረር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሙክታር ጀማል እንደገለጹት ስልጠናው ከሐረሪ ክልል፣ ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና ማያ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ 625 መረጃ ሰብሳቢዎች፣ ተቆጣጣሪዎች እና አስተባባሪዎች እየተሰጠ ነው።


በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ለ10 ቀናት በሚሰጠው በዚሁ ስልጠና በሶስት የተለያዩ ክፍሎች ላይ ያተኮረ ሙያዊ ስልጠና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

በዚህም በሐረሪ ክልል፣ ምስራቅ ሐረርጌ ዞንና ማያ ከተማ አስተዳደር ከተመረጡ 11ሺህ 567 የኢኮኖሚ ድርጅቶች የሰው ሃይላቸውን፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴያቸውንና ወጪና ገቢያቸውን ጨምሮ ሌሎችም መረጃዎች ይሰበሰባሉ ብለዋል።

እንደ አቶ ሙክታር ገለጻ ከጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ዋናው የመረጃ መሰብሰብ ስራ እንደሚገባም አክለዋል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዘርፈ ብዙና የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥናቶችን በማከናወን መረጃዎችን በመሰብሰብ ይተነትናል ያሉት ደግሞ የስልጠናው ዋና አስተባባሪ አቶ እንዳሻው ፈለቀ ናቸው።


ስልጠናው የኢኮኖሚ ድርጅቶችን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ግንዛቤን ለቆጣሪዎች በመስጠት ስራውን ለማሳካት ያለመ ነው ብለዋል።

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራም የአገራችንን የኢኮኖሚ ሃብት ደረጃ ለማወቅ እንዲሁም ድርጅቶች ያላቸውን የሰው ሃይልና ሌሎች መረጃዎቻቸውን ለመለየትና ለጥናትና ምርምር፣ ለፖሊሲ ዝግጅት በማዋል ዘርፈ ብዙ ጥቅም አለው ብለዋል።


ስልጠናውን እየተከታተሉ ከሚገኙት መካከል ማዓዛ ሀብታሙ እንደገለጸችው ስልጠናው የጠራ መረጃ በመሰብሰብ ለአገራዊ እድገት መሰረት እንዲጣል የሚያግዝ ነው ብላለች።

ስልጠናው በኢኮኖሚው ዘርፍ የተመዘገበውን ስኬት ለማስቀጠል ፋይዳው የጎላ ነው ያለው ደግሞ ሌላው ሰልጣኝ ሸምሸዲን አብዶ ነው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026