የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአፍሪካ ችግር ፈች የምርምር ውጤቶችን ለማውጣት በሀገራት መካከል ትብብርና ቅንጅት ያስፈልጋል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ችግር ፈች የምርምር ውጤቶችን ለማውጣት በሀገራት መካከል ትብብርና ቅንጅት ያስፈልጋል ሲሉ የምርምር ተቋማት ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች ገለጹ፡፡

የአፍሪካ ሕብረት ልማት ኤጀንሲ /AUDA-NEPAD/ ከአፍሪካ ሳይንስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሳምንት 2026 "የአፍሪካን መጻኢ ዕድል በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን መበየን" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል፡፡


የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ ባዮኢንፎርማቲክስ ኢንስቲትዩት የጤና መረጃ ሳይንስ ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ኒኪ ቲፊን እንዳሉት፤ በአፍሪካ ችግር ፈች የምርምር ሥራዎችን ለማከናወን ፈተናዎች ይበዛሉ፡፡

በአብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ተመራማሪዎች በጤና፣ በድህነት ቅነሳና መሰል መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰሯቸው የጥናትና ምርምር ስራዎች ተቀራራቢ ተግዳሮቶች እንዳሉባቸው ገልጸዋል፡፡

በአፍሪካ የጤና ዘርፍ ምርምርን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የቤተ ሙከራ ኬሚካል ግብዓትን ለማሳደግ የአምራች ኢንዱስትሪውን ማበረታታት ይገባል ብለዋል፡፡

ለዚህ ደግሞ የአስተሳሰብ አድማስን በማስፋት ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ወደ አፍሪካ ምድር እንዲመጡ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በአፍሪካ የካንሰር ምርምር ላይ የሚያተኩረው የየማቺ ባዮቴክኖሎጂ አንዱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ያው ቤዲያኮ በአፍሪካ ብዙ ተመራማሪዎች የሎጂስቲክስና የአቅርቦት ሰንሰለት ችግር እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡


በአሕጉሪቱ ከምርምር ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ሀገራት መካከል ያለውን ትብብርና ቅንጅት ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡

በአፍሪካ ለምርምር ሥራዎች የሚያገለግሉ ግብዓቶችን እንቅስቃሴ በማሳለጥ የዘርፉ ውጤታማነት ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የነቃ ተሳትፎ ለዘርፉ ዕድገት ወሳኝ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ አህጉራዊ አምራቾችን ማበረታታት ይገባልም ብለዋል፡፡


በኬንያ የናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ተመራማሪ ቪንሰንት ኦኩንጉ በበኩላቸው፤ በአፍሪካ በምርምር ተቋማት ያለው ቢሮክራሲ መስተካከል ያለበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የምርምር ስራዎች ብክነትን የሚቀንሱ፣ የአፍሪካን ችግሮች የለዩና ትኩረታቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ መሆን አለበት ብለዋል፡፡

ምርምር የምንሰራው የማህበረሰባችንን ችግር ለመፍታት ነው ያሉት ከፍተኛ ተመራማሪው፤ ምርምርን የቅንጦት ሥራ ማድረግ እንደማይገባም አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025