የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአፍሪካ ችግር ፈች የምርምር ውጤቶችን ለማውጣት በሀገራት መካከል ትብብርና ቅንጅት ያስፈልጋል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ችግር ፈች የምርምር ውጤቶችን ለማውጣት በሀገራት መካከል ትብብርና ቅንጅት ያስፈልጋል ሲሉ የምርምር ተቋማት ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች ገለጹ፡፡

የአፍሪካ ሕብረት ልማት ኤጀንሲ /AUDA-NEPAD/ ከአፍሪካ ሳይንስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሳምንት 2026 "የአፍሪካን መጻኢ ዕድል በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን መበየን" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል፡፡


የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ ባዮኢንፎርማቲክስ ኢንስቲትዩት የጤና መረጃ ሳይንስ ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ኒኪ ቲፊን እንዳሉት፤ በአፍሪካ ችግር ፈች የምርምር ሥራዎችን ለማከናወን ፈተናዎች ይበዛሉ፡፡

በአብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ተመራማሪዎች በጤና፣ በድህነት ቅነሳና መሰል መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰሯቸው የጥናትና ምርምር ስራዎች ተቀራራቢ ተግዳሮቶች እንዳሉባቸው ገልጸዋል፡፡

በአፍሪካ የጤና ዘርፍ ምርምርን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የቤተ ሙከራ ኬሚካል ግብዓትን ለማሳደግ የአምራች ኢንዱስትሪውን ማበረታታት ይገባል ብለዋል፡፡

ለዚህ ደግሞ የአስተሳሰብ አድማስን በማስፋት ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ወደ አፍሪካ ምድር እንዲመጡ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በአፍሪካ የካንሰር ምርምር ላይ የሚያተኩረው የየማቺ ባዮቴክኖሎጂ አንዱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ያው ቤዲያኮ በአፍሪካ ብዙ ተመራማሪዎች የሎጂስቲክስና የአቅርቦት ሰንሰለት ችግር እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡


በአሕጉሪቱ ከምርምር ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ሀገራት መካከል ያለውን ትብብርና ቅንጅት ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡

በአፍሪካ ለምርምር ሥራዎች የሚያገለግሉ ግብዓቶችን እንቅስቃሴ በማሳለጥ የዘርፉ ውጤታማነት ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የነቃ ተሳትፎ ለዘርፉ ዕድገት ወሳኝ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ አህጉራዊ አምራቾችን ማበረታታት ይገባልም ብለዋል፡፡


በኬንያ የናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ተመራማሪ ቪንሰንት ኦኩንጉ በበኩላቸው፤ በአፍሪካ በምርምር ተቋማት ያለው ቢሮክራሲ መስተካከል ያለበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የምርምር ስራዎች ብክነትን የሚቀንሱ፣ የአፍሪካን ችግሮች የለዩና ትኩረታቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ መሆን አለበት ብለዋል፡፡

ምርምር የምንሰራው የማህበረሰባችንን ችግር ለመፍታት ነው ያሉት ከፍተኛ ተመራማሪው፤ ምርምርን የቅንጦት ሥራ ማድረግ እንደማይገባም አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026