የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞችን መረጃ የሚያዘምን ፕሮጀክት ማስጀመሩን አስታወቀ

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤የካቲት 18 /2018 (ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች መረጃ የሚያዘምን የፕሮጀክት ሙከራ ትግበራ ማስጀመሩን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የደንበኞች አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሥርዓት የተደገፉ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በማስመልከት ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥቷል።


መግለጫውንም በባለሥልጣኑ የአገልግሎት ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ አርጋው እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወካይና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ገረመው ሳህሌ በጋራ ሰጥተዋል።

አቶ ሞገስ አርጋው በዚህ ወቅት፤ የደንበኞችን የውሃ አቅርቦት አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማስተሳሰር የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የደንበኞች መረጃ ማዘመን ፕሮጀክት ትግበራም የቢል፣ ማህደርና የመሬት መረጃዎችን በማጣጣም ዘመናዊ ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና የውሃ ብክነትን የሚቀንስ አገልግሎቶችን ለመስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማም የተሟላ፤ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ በማደራጀት አሠራርን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተቀላጠፈ የመስመር ላይ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወካይና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ገረመው ሳህሌ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የውሃ አገልግሎቶችን የሚያሳልጥ የስማርት ሲቲ ግንባታ አካል መሆኑን ገልጸዋል።

የፕሮጀክቱም የውሃና ሳኒቴሽን ሥርዓትን በማዘመን የባለስልጣኑን ተለምዷዊ አገልግሎት አሰጣጥ መቀየር የሚስችል ምኅዳር የሚፈጥርና ዘላቂነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች መረጃ የሚያዘምነው ፕሮጀክትም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 እንዲሁም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በይፋ የተጀመረ ሲሆን በቀጣይም ተደራሽነቱን ለማስፋት እንደሚሰራ ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026