🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18 /2018 (ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች መረጃ የሚያዘምን የፕሮጀክት ሙከራ ትግበራ ማስጀመሩን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የደንበኞች አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሥርዓት የተደገፉ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በማስመልከት ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውንም በባለሥልጣኑ የአገልግሎት ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ አርጋው እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወካይና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ገረመው ሳህሌ በጋራ ሰጥተዋል።
አቶ ሞገስ አርጋው በዚህ ወቅት፤ የደንበኞችን የውሃ አቅርቦት አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማስተሳሰር የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የደንበኞች መረጃ ማዘመን ፕሮጀክት ትግበራም የቢል፣ ማህደርና የመሬት መረጃዎችን በማጣጣም ዘመናዊ ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና የውሃ ብክነትን የሚቀንስ አገልግሎቶችን ለመስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማም የተሟላ፤ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ በማደራጀት አሠራርን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተቀላጠፈ የመስመር ላይ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወካይና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ገረመው ሳህሌ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የውሃ አገልግሎቶችን የሚያሳልጥ የስማርት ሲቲ ግንባታ አካል መሆኑን ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱም የውሃና ሳኒቴሽን ሥርዓትን በማዘመን የባለስልጣኑን ተለምዷዊ አገልግሎት አሰጣጥ መቀየር የሚስችል ምኅዳር የሚፈጥርና ዘላቂነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች መረጃ የሚያዘምነው ፕሮጀክትም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 እንዲሁም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በይፋ የተጀመረ ሲሆን በቀጣይም ተደራሽነቱን ለማስፋት እንደሚሰራ ተጠቁሟል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026