🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18 /2018 (ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች መረጃ የሚያዘምን የፕሮጀክት ሙከራ ትግበራ ማስጀመሩን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የደንበኞች አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሥርዓት የተደገፉ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን በማስመልከት ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውንም በባለሥልጣኑ የአገልግሎት ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ አርጋው እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወካይና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ገረመው ሳህሌ በጋራ ሰጥተዋል።
አቶ ሞገስ አርጋው በዚህ ወቅት፤ የደንበኞችን የውሃ አቅርቦት አገልግሎቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማስተሳሰር የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የደንበኞች መረጃ ማዘመን ፕሮጀክት ትግበራም የቢል፣ ማህደርና የመሬት መረጃዎችን በማጣጣም ዘመናዊ ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና የውሃ ብክነትን የሚቀንስ አገልግሎቶችን ለመስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማም የተሟላ፤ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ በማደራጀት አሠራርን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተቀላጠፈ የመስመር ላይ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወካይና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ገረመው ሳህሌ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱ የውሃ አገልግሎቶችን የሚያሳልጥ የስማርት ሲቲ ግንባታ አካል መሆኑን ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱም የውሃና ሳኒቴሽን ሥርዓትን በማዘመን የባለስልጣኑን ተለምዷዊ አገልግሎት አሰጣጥ መቀየር የሚስችል ምኅዳር የሚፈጥርና ዘላቂነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የደንበኞች መረጃ የሚያዘምነው ፕሮጀክትም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 እንዲሁም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በይፋ የተጀመረ ሲሆን በቀጣይም ተደራሽነቱን ለማስፋት እንደሚሰራ ተጠቁሟል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026