የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ አስታወቁ።

በ2014 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተጀመረው የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር የዲጂታል መሠረተ ልማትን ለማሳለጥ እየተሰራ ይገኛል።

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ160 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ደምበኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት ተሰጥቷል

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ አካታች እንዲሆን ከተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንዲሰራ ተደርጓል።

በዚህም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን ገልፀው፤ የምዝገባ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ወዲህ 36 ሚሊዮን ዜጎች ተመዝግበው የመታወቂያው ባለቤት መሆናቸውን ገልጸዋል።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የአገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ እና ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ዓይነተኛ ሚና እያበረከተ እንደሆነ ጠቁመው፤ በተለይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።

ለአብነትም ፋይዳን ከአርሶ አደሩ የመሬት ባለቤትነት ጋር ማስተሳሰር በርካታ ዜጎች እንዲመዘገቡ ከማድረግ ባለፈ አርሶ አደሩ ይዞታውን አስይዞ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኝ እና ማሳውን በአግባቡ ለማስተዳደር እንደሚያግዘው አንስተዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስካሁን ከ250 ሺህ በላይ ዜጎች የተመዘገቡ ሲሆን አፈጻጸሙን ለማሻሻል የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚያስፈልግም አስተባባሪው አስታውቀዋል።

በክልሉ የመቶ ፐርሰንት ግብ አፈጻጸም ዝቅተኛ በመሆኑ ከተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በማስተሳሰር ዕቅዱን ማሳካት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሬትና ህብረት ስራ ማደራጃ ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ብሔራዊ መታወቂያ ለገጠር መሬት ባለይዞታዎች" በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ መካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026