የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳለጥ ወጣቶችን በቴክኖሎጂ የማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ የካቲት 20/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳለጥ ወጣቶችን በቴክኖሎጂ ለማብቃት ስራ ትኩረት መሰጠቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) አስታወቁ።

የሰውሰራሽ አስተውሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኦሮሚያ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር በአምቦ ከተማ ያስገነባው የወጣቶች ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከል እና የአምቦ ስታርት አፕ ማዕከል ተመርቋል።


በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ እና ሌሎች የፌዴራል እና የክልል አመራሮች ተገኝተዋል።

በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማስቀጠል ወጣቶችን በቴክኖሎጂ፣ በሳይንስና በፈጠራ ለማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።

ዛሬ በአምቦ ከተማ አገልግሎት የጀመረው ማዕከልም በአገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የኢኖቬሽን ሥነ-ምህዳር የማጠናከርና የቴክኖሎጂ ክፍተቶችን ለመሙላት ያግዛል ብለዋል።


መሰል የኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ማዕከላት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገንብተው የዜጎችን ችግር እየፈቱ መሆኑን ጠቅሰው የአምቦው ማዕከልም ወጣቶችን በቴክኖሎጂ በማብቃት የማኅበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የፈጠራ ሥራዎች የሚፈልቁበት ይሆናል ነው ያሉት።

የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው፤ የአንድን ሀገር ዕድገት ማፋጠን የሚቻለው በቴክኖሎጂ ማገዝ ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል።


የክልሉ መንግሥት ግብርናንና ሌሎች ዘርፎችን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻልና የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግብ ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የአምቦ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃጫሉ ገመቹ፤ ማዕከሉ ወጣቶች የሚዝናኑበት ብቻ ሳይሆን፣ ዕውቀታቸውን ወደ ተግባር በመለወጥ ማኅበረሰባቸውን የሚያገለግሉበት የፈጠራ ማዕከል መሆኑን አብራርተዋል።


በማዕከሉ የቴክኖሎጂ ሥልጠና የወሰዱ ወጣቶች በበኩላቸው፣ ባገኙት ዕውቀት ተጠቅመው የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።


በተለይም የድረ-ገጽ ማበልጸግ ሥልጠና በመውሰድ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ማኅበረሰብን በፈጠራ ለማገዝ መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026