የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ያሳዩትን አኩሪ ገድል የዘመኑ ትውልድ በልማቱ ሊደግመው ይገባል

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ያሳዩትን አኩሪ ገድል የዘመኑ ትውልድ በልማቱ ሊደግመው ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለጹ።

የዓድዋን ድል ስናከብር የተሰጠንን ሀገራዊ ተልእኮ በላቀ ብቃትና ዝግጁነት ለመወጣት ዳግም ቃል በመግባት ነው

’’ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ’’ በሚል መሪ ሃሳብ 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል በጋምቤላ ከተማ ተከብሯል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በክብረ በዓሉ ላይ እንዳሉት፤ ቀደምት አባቶች በአንድነትና በህብረት በዓድዋ ያሳዩት ድል ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን ጭምር ታላቅ የነፃነት ቀንዲል ነው።


በዘመኑ ኢትዮጵያውያን ለዓድዋ ታሪካዊ ድል የበቁት በአንድነትና በህብረት በመታገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም የዘመኑ ትውልድ የአባቶቹን የአብሮነት፣ የአንድነትና የትብብር እሴት በማጎልበት በክልሉ ብሎም በሀገሪቱ የታለሙትን የልማት ግቦች ለማሳካት በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

የዘንድሮው የዓድዋ ድል በዓል በርካታ የልማት ጅምሮችና ስኬቶች እየተመዘገቡ ባሉበት ወቅት መከበሩ ልዩ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ አቶ ቱት ጆክ በበኩላቸው፤ የዓድዋ ድል ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ሉዓላዊነት ላለማስደፈር ጽናታቸውና አይበገሬነታቸውን ለዓለም ማህበረሰብ ያሳዩበት ታሪካዊ ቀን ነው ብለዋል።

በመሆኑም የዓድዋ ድል ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን የአሸናፊነትና የጥንካሬያችን ማሳያ ታሪካዊ የድል በዓል ነው ሲሉ ገልጸዋል።


በክብረ በዓሉ ላይ የታደሙት የጸጥታ አካላት በሰጡት አስተያየት፤ በጀግኞች አባቶች ተከብራና ታፍራ የቆየችው ኢትዮጵያ ዛሬም በእኛ በልጆቿ ክብሯና ሉዓላዊነቷ ጸንቶ ይቀጥላል ብለዋል።

የዓድዋ ድል ለዘመኑ ትውልድ ጽናትን፣ አንድነትን፣ ህብረትንና አልሸነፍ ባይነትን ያወረሰ ታሪካዊ የድል ቀን መሆኑን የጸጥታ አካላቱ ገልጸዋል።

በክብረ በዓሉ ላይ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች የታደሙ ሲሆን የክልልና የፌዴራል የጸጥታ አካላት የሰልፍ ትርኢት አሳይተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026