🔇Unmute
ጋምቤላ ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ያሳዩትን አኩሪ ገድል የዘመኑ ትውልድ በልማቱ ሊደግመው ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለጹ።
የዓድዋን ድል ስናከብር የተሰጠንን ሀገራዊ ተልእኮ በላቀ ብቃትና ዝግጁነት ለመወጣት ዳግም ቃል በመግባት ነው
’’ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ’’ በሚል መሪ ሃሳብ 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል በጋምቤላ ከተማ ተከብሯል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በክብረ በዓሉ ላይ እንዳሉት፤ ቀደምት አባቶች በአንድነትና በህብረት በዓድዋ ያሳዩት ድል ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን ጭምር ታላቅ የነፃነት ቀንዲል ነው።

በዘመኑ ኢትዮጵያውያን ለዓድዋ ታሪካዊ ድል የበቁት በአንድነትና በህብረት በመታገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም የዘመኑ ትውልድ የአባቶቹን የአብሮነት፣ የአንድነትና የትብብር እሴት በማጎልበት በክልሉ ብሎም በሀገሪቱ የታለሙትን የልማት ግቦች ለማሳካት በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
የዘንድሮው የዓድዋ ድል በዓል በርካታ የልማት ጅምሮችና ስኬቶች እየተመዘገቡ ባሉበት ወቅት መከበሩ ልዩ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ አቶ ቱት ጆክ በበኩላቸው፤ የዓድዋ ድል ኢትዮጵያውያን የሀገራቸውን ሉዓላዊነት ላለማስደፈር ጽናታቸውና አይበገሬነታቸውን ለዓለም ማህበረሰብ ያሳዩበት ታሪካዊ ቀን ነው ብለዋል።
በመሆኑም የዓድዋ ድል ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን የአሸናፊነትና የጥንካሬያችን ማሳያ ታሪካዊ የድል በዓል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በክብረ በዓሉ ላይ የታደሙት የጸጥታ አካላት በሰጡት አስተያየት፤ በጀግኞች አባቶች ተከብራና ታፍራ የቆየችው ኢትዮጵያ ዛሬም በእኛ በልጆቿ ክብሯና ሉዓላዊነቷ ጸንቶ ይቀጥላል ብለዋል።
የዓድዋ ድል ለዘመኑ ትውልድ ጽናትን፣ አንድነትን፣ ህብረትንና አልሸነፍ ባይነትን ያወረሰ ታሪካዊ የድል ቀን መሆኑን የጸጥታ አካላቱ ገልጸዋል።
በክብረ በዓሉ ላይ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች የታደሙ ሲሆን የክልልና የፌዴራል የጸጥታ አካላት የሰልፍ ትርኢት አሳይተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026