የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ለሀገራዊ ደህንነትና ለቀጣናዊ ሰላም መከበር ወሳኝ ነው

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ሀገራዊ ደህንነትን ለማረጋገጥና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር ወሳኝ መሆኑን የቀድሞ የባህር ኃይል አባልና የታሪክ ምሁራን ገለጹ።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ በቀጣናው ያለው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ጥረት እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያና ቀይ ባህር ለዘለዓለም ተነጣጥለው እንደማይኖሩ በማንሳት፥ ፍትሐዊ ጥያቄያችን በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በድርድር መርህ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረታችን ይቀጥላል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ጥያቄ ፍትሐዊ ካልሆነ በዓለም ላይ ፍትሕ የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ መልስ ማግኘቱ አይቀሬ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የቀድሞ የባህር ኃይል አባል ጁኒየር ሌተናንት ሀለፎም መሰለ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በሴራ የባህር በር አልባ እንድትሆን ከመደረጓ በፊት በአካባቢው ላይ ጠንካራና ተፅዕኖ ፈጣሪ የባህር ኃይል ነበራት።


በዚህም በቀይ ባህር ቀጣና የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሀገራት የንግድ መርከቦች ጭምር ደህንነታቸው ተጠብቆ ሰላማዊ ጉዞ እንዲያደርጉ ሀገሪቱ ወሳኝ ሚና ስትጫወት መቆየቷን አስታውሰዋል።

የባህር ኃይሉ በተለይም ሕገ-ወጥ ንግድ፣ ኮንትሮባንድን፣ የባህር ላይ ሽፍቶችን እንቅስቃሴዎች በመግታት ለቀጣናው ሰላምና ደህንነት ዋስትና ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል።

በሀገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የህልውና ጉዳይ ለሆነው የባህር በር ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ ለማግኘት ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የባህር በር በማጣቷ ምክንያት ከፍተኛ ዋጋ የከፈለች መሆኑን ጠቅሰው፤ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀደም ብሎ ሊነሳ የሚገባው እንደነበር አንስተዋል።


የታሪክ ምሁርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ በበኩላቸው፤ የጥንቶቹ የዳማትና የአክሱም ሥልጣኔዎች ከባህር በር ጋር በነበራቸው ቁርኝት የገነኑ እንደነበሩ በታሪካዊ ማስረጃነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለሷ ሀገራዊ ተጽዕኖዋን ከመጨመሩ በላይ ብሔራዊ ጥቅሟን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ጉልህ አሻራ እንደሚያሳርፍ አክለዋል።


የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ድልና በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያሳዩትን ጽኑ አንድነት የባህር በር ጥያቄው ግቡን እንዲመታና ብሔራዊ ጥቅሟ እንዲከበር በአንድነት በመቆም ሊደግሙት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026