የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ ፤የካቲት 29/2018 (ኢዜአ):-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

የክልሉ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ግብረ-ሃይል የግማሽ ዓመት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት በክልሉ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡

ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በፈጠረው ምቹ ሁኔታ በገቢና ወጪ ንግድ ሥራ ላይ ሰፊ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል።

ይሁንና ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች በኢኮኖሚው ውስጥ ጤናማ ግብይት እንዳይካሄድ ዘርፈ ብዙ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይ ነዳጅን ጨምሮ በድጎማ የሚመጡ ሸቀጦችን ህዝቡ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንዳይጠቀም ጫና እያሳደሩ ይገኛሉ ብለዋል።

እንደ አቶ ጥላሁን ገለጻ ጥራትና ብቃቱ ያልተረጋገጠ ህገወጥ ምርት ለማህበራዊ ቀውስ ከመዳረግ ባለፈ የተለያዩ ግጭቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ ፖለቲካዊ ቀውስ ያስከትላል።

በክልሉ የተቋቋመው የኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ግብረ-ሃይል የተቀናጀ ቁጥጥር በማድረግ ጤናማና ፍትሃዊ የንግድ ሥርአት እንዲኖር ሃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስበዋል።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሰናይት ሰለሞን በበኩላቸው እንዳሉት በግማሽ ዓመቱ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ መቆጣጠርን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች ውጤት ተመዝግቧል።

ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የህግ የበላይነትን በመሸርሸርና ገበያን በማዛባት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ስለሚያስከትል የመከላከል ሥራው በቅንጅት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ባለፉት ስድስት ወራት የኑሮ ውድነት ለመፍጠር በሸቀጦችና ሌሎች ምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 21ሺህ 600 የንግድ ድርጅቶች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም ተናግረዋል።

ከነዳጅ ጋር በተያያዘ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ መያዙን የገለጹት ወይዘሮ ሰናይት፣ በነዳጅ ግብይት ህግ በተላለፉ 15 ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

ግብረ-ሃይሉ ባደረገው ቁጥጥርም ከ910 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም 28 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መድሃኒትና ምግቦችን በመያዝ በህዝብ ላይ ሊደርስ የነበረን የጤና ችግር መቆጣጠር ተችሏል ብለዋል።

በመድረኩ የክልል፣ የዞኖችና የከተሞች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና የፀጥታ አካላት የተሳተፉ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይም ውይይት ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025