የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአዲስ አበባ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያስቀጥል አስቻይ ምኅዳር ተፈጥሯል 

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያስቀጥል አስቻይ የአሰራር ምኅዳር መፈጠሩን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ገለጹ።

በክልሉ የእምነት ተቋማት ለሰላምና ትውልድ ግንባታ ያላቸውን አበርክቶ ሊያጠናክሩ ይገባል

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ከዛሬ መጋቢት 02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የሥራ አውደ ርዕይ ከፍቷል።

"የግል ዘርፍ ተሳትፎ፤ የብቁ ወጣቶች ማንሰራራት ለሀገር ልዕልና" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀውን የሥራ አውደ ርዕይ ከ11 ሺህ በላይ ሥራ ፈላጊ ወጣቶችና ሴቶች እንደሚጎበኙት ይጠበቃል።

የሥራ አውደ ርዕዩ 6 ሺህ የሚሆኑ ሥራ ፈላጊ ወጣቶችና ሴቶች ቀጥተኛ ሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚሆኑበት መርሃ ግብር የሚያመቻች መሆኑ ተገልጿል።

አውደ ርዕዩን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ከፍተውታል።

በዚሁ ጊዜ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ እንዳሉት፤ የአዲስ አበባ ከተማ ፈጣን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድገት ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት መሰረት እየጣለ ነው።

ከተማ አስተዳደሩ ሥራ ፈላጊዎችን በማደራጀትና ከሥራ ቀጣሪዎች ጋር በማገናኘት የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያስቀጥል አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።

በቴክኖሎጂ ዘርፍም ሥራ ፈላጊዎችና ቀጣሪዎችን የሚያገናኝ ምቹ ምህዳር መፍጠር መቻሉን አስረድተዋል።

በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ለሶስት ቀናት የሚቆየው የሥራ አውደ ርዕይም የወጣቶችንና ሴቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማሻሻል ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አንስተዋል።

የአዲስ አበባ የ24/7 የሥራ ባህልም የከተማዋን ልማትና ዕድገት በማስቀጠል የበርካታ ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትልና የምግብ ዋስትና ዘርፍ ኃላፊ አስፋው ለገሰ በበኩላቸው፤ በመዲናዋ በሰባት ወራት ውስጥ ከ280 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በሥራ አውደ ርዕዩ የሚሳተፉ ከ200 በላይ ቀጣሪ ድርጅቶች የሚያስፈልጋቸውን የሰለጠነ የሰው ሃይል በመመልመል በርካታ ወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026