የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የኃይል ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት በትኩረት እየሰራች ነው-ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የኃይል ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት በትኩረት እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ኃብት በመጠቀም በካይ ያልሆኑ የኃይል ምንጮችን ለማልማት የረጅም ጊዜ ስትራቴጂ ነድፋ እየሰራች የምትገኝ ሲሆን የውሃ ኃይል፣ የንፋስና ፀሐይ ኃይል እንዲሁም የጂኦተርማል ተጠቃሾች ናቸው፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት ከምትጠቀመው አጠቃላይ የኃይል ምንጭ ውስጥ ከ96 በመቶ በላይ የሚሆነው በካይ ካልሆኑና ታዳሽ ከሆኑ ምንጮች የሚገኝ ነው።

ይህም ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ኢነርጂ ልማት ረገድ ቀዳሚ ተጠቃሽ ሀገር እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።

የውሃ ኃይል (Hydro) ትልቁን የኃይል ድርሻ የሚይዝ መሆኑን ጠቅሰው፥ የፀሐይና የንፋስ ኃይል ቴክኖሎጂዎችም በስፋት ወደ ስራ እየገቡ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ይህ ስኬት መንግስት ሀብቱን ወደዚህ ዘርፍ ለማዞር ባሳለፈው ፖሊሲ ተኮር ውሳኔ የተገኘ መሆኑን ጠቁመው፥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የዚህ ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ትልቁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

መንግስት የዜጎችን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በአረንጓዴ ኢነርጂ ልማት ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ከሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኘው አጠቃላይ የኃይል መጠን ከ10 ጊጋ ዋት በላይ መድረሱ ከፍተኛ ሀገራዊ አቅም መፈጠሩን ያሳያል ብለዋል።

የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስና የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ ከነዳጅ ነፃ የሆኑ አማራጮችን ማስፋፋት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አሳስበው በየደረጃው የታቀዱ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026