🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የ'አዲስ መሶብ' የአንድ ማዕከል የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት የመልካም አስተዳደር ውጤታማነትን እያረጋገጠ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 3ኛውን የ'አዲስ መሶብ' ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት የልደታ ቅርንጫፍን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

በዚሁ ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደተናገሩት፤ የመንግስትን አገልግሎቶች ጥራትና ውጤታማነት የሚያስጠብቅ አስቻይ ምኅዳር እየተፈጠረ ነው።
በዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነት የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የተገልጋዮችን እርካታ እያሻሻለ ይገኛል ብለዋል።
በመሶብ የአንድ ማዕከል የሚሰጡ አገልግሎቶች ጥራትና ውጤታማነትን በማስጠበቅ ብልሹ አሰራሮችን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ማስቻሉን ተናግረዋል።

በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የተገኘው ተጨባጭ ውጤት ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ለዜጎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መፍትሔ መስጠቱን ገልጸዋል።
በመዲናዋ የተገነቡ የአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከላት የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎት በማፋጠን የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በቀጣይም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ የተገልጋዮችን እርካታ የማሻሻል ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026