የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሀገራትና ዓለም አቀፍ ተቋም ጋር የተደረጉ አራት የብድር ስምምነቶችን አጸደቀ

Mar 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፈረንሳይ፣ኮሪያና ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተደረጉ አራት የብድር ስምምነቶችን መርምሮ አጽድቋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በኮሪያ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ መካከል ለህክምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጀክት ምዕራፍ-2 እና ለብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ሥርዓት ማስፋፊያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የተደረገውን የብድር ስምምነት አጽድቋል።

በተጨማሪም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ መካከል ለታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ዘላቂ ኃይልና ዲጂታላይዜሽን ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የብድር ስምምነትን አጽድቋል።

በሶስተኛነትም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል ለከተማ ልማታዊ ሴፍትኔትና ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የብድር ስምምነትን አጽድቋል፡፡

የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ መርምሮ ለፕላን፣በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መምራትም ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባ ከመከረባቸው ጉዳዮች አንዱ ነው።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ፤ የሕክምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፕሮጀክት ምዕራፍ-2 ማስፈጸሚያ የብድር ስምምነቱ ከሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ጋር የተጣጣመ መሆኑን ገልጸዋል።


አነስተኛ ወለድ ምጣኔ ያለው የብድር ስምምነቱም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፤ ስምምነቶቹ ዘላቂ የልማት ግቦችን የሚያሳልጡና ከኢትዮጵያ የብድር አስተዳደር ስርዓት ጋር የተጣጣሙ ናቸው ብለዋል።


የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅም ተቋሙ ወቅቱን የዋጀና የተሳለጠ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በብድር ስምምነቶችና የጉምሩክ አዋጁን እንደገና ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ ላይ በሰጡት አስተያየት፤በብድር የሚገኝ ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የብድር ስምምነቶቹም የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ትልቅ አቅም እንደሚሆኑም ገልጸዋል፡፡


የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው፤በብድር ስምምነት የተገኙ ሃብቶች ላይ ጥብቅ የፕሮጀክት አፈፃጸም ቁጥጥር በማድረግ ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲውሉ ይደረጋል ብለዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን በበኩላቸው፤ የብድር ስምምነቶቹ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ለዘላቂ የልማት ግቦች ውጤታማነት ጉልህ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026