🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት እንደሚጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ፤ እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸው ፋይዳ በጥልቀት ተዳሷል።
ኢትዮጵያ ውብ፣ ታላቅና በስልጣኔ ቀደምት የሆነች ሀገር ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ የራሷ አቆጣጠር ያላት፣ በአፍሪካ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ ሀገር፣ የሰው ልጅ መገኛ ቡናን ለዓለም የሰጠች ሀገር መሆኗንም አውስተዋል።
ይህም ኢትዮጵያ ተቀባይ ብቻ ሳትሆን ለዓለም አስተዋጽኦ ማድረግ የሚያስችል ብቃት ያለው ህዝብ እንዳላት የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያን ከአጭር ጊዜ ይልቅ አርቆ በማየትና በማሰብ በትብብር ከገነባን ለብዙዎች ብርቅ ለብዙዎች መጠለያ ለብዙዎች መሸሸጊያ የምትሆን ሀገር መፍጠር ይቻላል ነው ያሉት።
ከ1 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ፍልሰተኞችን ተቀብላ ማስተናገዷን ጠቅሰው ሀገርን በወግ እና በስርዓት መገንባት ከተቻለ ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ አድርጎ መስራት እንደሚቻል አመልክተዋል።
የሰው ልጅ የተሰጠው ጊዜ ውስን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠን ጊዜ በተገቢው ሁኔታ መስራትና ለልጆች የሚታወስና የሚጠቅም ነገር ማድረግ አለብን ብለዋል።
በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት ጥለን እናልፋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካውም በኢኮኖሚውም በዲፕሎማሲውም በወታደራዊ አቅሙም ለትውልድ አስቻይ የሆነ መሰረት ጥለን እንደምናልፍ ተስፋ አለኝ ብለዋል።
ይሄ ነገር እንዳይሳካ የሚያደናቅፉ ኃይሎች ሊኖሩ ቢችሉም እኛ እንቅፋቶቻችንን ከመንገዶቻችን እያስወገድን ያሰብነውን ለማሳካት በተሰጠን ጊዜ ቀንና ለሊት እንተጋለን ልጆቻችን ያስቀጥሉታል ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ ድንቅ መሆኗን ታሪክ ጠገብ መሆኗን ሀብታም መሆኗን በንግግር ሳይሆን በተግባር ገልጠን የምናሳይበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት እና የግዙፍ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በስኬትና በለውጥ ላይ የምትገኝበት ወቅት መሆኑንም ገልጸዋል።
የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተግተን ከሰራን የወደፊቷ ያማረ እና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር እንደሚቻል ተናግረዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026