🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት እንደሚጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ፤ እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸው ፋይዳ በጥልቀት ተዳሷል።
ኢትዮጵያ ውብ፣ ታላቅና በስልጣኔ ቀደምት የሆነች ሀገር ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ የራሷ አቆጣጠር ያላት፣ በአፍሪካ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ ሀገር፣ የሰው ልጅ መገኛ ቡናን ለዓለም የሰጠች ሀገር መሆኗንም አውስተዋል።
ይህም ኢትዮጵያ ተቀባይ ብቻ ሳትሆን ለዓለም አስተዋጽኦ ማድረግ የሚያስችል ብቃት ያለው ህዝብ እንዳላት የሚያመላክት እንደሆነም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያን ከአጭር ጊዜ ይልቅ አርቆ በማየትና በማሰብ በትብብር ከገነባን ለብዙዎች ብርቅ ለብዙዎች መጠለያ ለብዙዎች መሸሸጊያ የምትሆን ሀገር መፍጠር ይቻላል ነው ያሉት።
ከ1 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ፍልሰተኞችን ተቀብላ ማስተናገዷን ጠቅሰው ሀገርን በወግ እና በስርዓት መገንባት ከተቻለ ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ አድርጎ መስራት እንደሚቻል አመልክተዋል።
የሰው ልጅ የተሰጠው ጊዜ ውስን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠን ጊዜ በተገቢው ሁኔታ መስራትና ለልጆች የሚታወስና የሚጠቅም ነገር ማድረግ አለብን ብለዋል።
በኢትዮጵያ በሁሉም መስክ አስተማማኝ መሰረት ጥለን እናልፋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካውም በኢኮኖሚውም በዲፕሎማሲውም በወታደራዊ አቅሙም ለትውልድ አስቻይ የሆነ መሰረት ጥለን እንደምናልፍ ተስፋ አለኝ ብለዋል።
ይሄ ነገር እንዳይሳካ የሚያደናቅፉ ኃይሎች ሊኖሩ ቢችሉም እኛ እንቅፋቶቻችንን ከመንገዶቻችን እያስወገድን ያሰብነውን ለማሳካት በተሰጠን ጊዜ ቀንና ለሊት እንተጋለን ልጆቻችን ያስቀጥሉታል ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ ድንቅ መሆኗን ታሪክ ጠገብ መሆኗን ሀብታም መሆኗን በንግግር ሳይሆን በተግባር ገልጠን የምናሳይበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት እና የግዙፍ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በስኬትና በለውጥ ላይ የምትገኝበት ወቅት መሆኑንም ገልጸዋል።
የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተግተን ከሰራን የወደፊቷ ያማረ እና የበለጸገች ኢትዮጵያን መፍጠር እንደሚቻል ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026