🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦መንግስት የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስታት የመሰረተ ልማት ግንባታን ለገበያ ከመስጠት ይልቅ በዘርፉ መዋዕለ ንዋይ የማፍሰሳቸው ተገቢነትን በተመለከተ በሰጡት ማብራርያ፤ በዓለም ላይ መንግስት ሳይገባበት የተገነባ መሰረተ ልማት አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡
ሀገራት መሰረተ ልማቶች ከተገነቡና የማህበረሰብ እውቀትና ሀብት ከሆኑ በኃላ ገንዘብ እንዲያመጡ ወደ ግል ማሸጋገር እንደሚፈልጉም አንስተዋል፡፡
ለዚህም ከዛሬ 50 ዓመት በፊት የግል ሳተላይት የሚያመጥቅ እንዳልነበረ እና አሁን ላይ ከሀገራት ባለፈ ግለሰቦችና ኩባንያዎች ጭምር እንደሚያመጥቁ ለአብነት አውስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከፍተኛ መዋዕለንዋይ የሚፈልጉ በመሆኑ ለባለሀብት መስጠት አዳጋች መሆኑንና ነገር ግን ወደፊት ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
በዘርፉ መንግስት መሳተፉ ለኢኮኖሚው ሞተር በመሆኑ የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ ወደፊትም በሰፊው መሳተፉ የሚቀር እንዳልሆነም ጠቁመዋል፡
ይህም የገቢ አቅምን ለመጨመር፤ኢኮኖሚያዊ ፍትሃዊነትን እንዲሁም የኑሮ ጥራትን ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል፡፡
ወደፊትም ማህበረሰቡን በብዙ መልኩ የሚጠቅም በመሆኑ መንግስት የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026