🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦መንግስት የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስታት የመሰረተ ልማት ግንባታን ለገበያ ከመስጠት ይልቅ በዘርፉ መዋዕለ ንዋይ የማፍሰሳቸው ተገቢነትን በተመለከተ በሰጡት ማብራርያ፤ በዓለም ላይ መንግስት ሳይገባበት የተገነባ መሰረተ ልማት አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡
ሀገራት መሰረተ ልማቶች ከተገነቡና የማህበረሰብ እውቀትና ሀብት ከሆኑ በኃላ ገንዘብ እንዲያመጡ ወደ ግል ማሸጋገር እንደሚፈልጉም አንስተዋል፡፡
ለዚህም ከዛሬ 50 ዓመት በፊት የግል ሳተላይት የሚያመጥቅ እንዳልነበረ እና አሁን ላይ ከሀገራት ባለፈ ግለሰቦችና ኩባንያዎች ጭምር እንደሚያመጥቁ ለአብነት አውስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከፍተኛ መዋዕለንዋይ የሚፈልጉ በመሆኑ ለባለሀብት መስጠት አዳጋች መሆኑንና ነገር ግን ወደፊት ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
በዘርፉ መንግስት መሳተፉ ለኢኮኖሚው ሞተር በመሆኑ የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ ወደፊትም በሰፊው መሳተፉ የሚቀር እንዳልሆነም ጠቁመዋል፡
ይህም የገቢ አቅምን ለመጨመር፤ኢኮኖሚያዊ ፍትሃዊነትን እንዲሁም የኑሮ ጥራትን ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል፡፡
ወደፊትም ማህበረሰቡን በብዙ መልኩ የሚጠቅም በመሆኑ መንግስት የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026