የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

መንግስት የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦መንግስት የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመት እና የኮሪደር ልማት በሚል መሪ ሐሳብ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስታት የመሰረተ ልማት ግንባታን ለገበያ ከመስጠት ይልቅ በዘርፉ መዋዕለ ንዋይ የማፍሰሳቸው ተገቢነትን በተመለከተ በሰጡት ማብራርያ፤ በዓለም ላይ መንግስት ሳይገባበት የተገነባ መሰረተ ልማት አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡

ሀገራት መሰረተ ልማቶች ከተገነቡና የማህበረሰብ እውቀትና ሀብት ከሆኑ በኃላ ገንዘብ እንዲያመጡ ወደ ግል ማሸጋገር እንደሚፈልጉም አንስተዋል፡፡

ለዚህም ከዛሬ 50 ዓመት በፊት የግል ሳተላይት የሚያመጥቅ እንዳልነበረ እና አሁን ላይ ከሀገራት ባለፈ ግለሰቦችና ኩባንያዎች ጭምር እንደሚያመጥቁ ለአብነት አውስተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከፍተኛ መዋዕለንዋይ የሚፈልጉ በመሆኑ ለባለሀብት መስጠት አዳጋች መሆኑንና ነገር ግን ወደፊት ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

በዘርፉ መንግስት መሳተፉ ለኢኮኖሚው ሞተር በመሆኑ የዜጎችን ህይወት በሚቀይር መልኩ ወደፊትም በሰፊው መሳተፉ የሚቀር እንዳልሆነም ጠቁመዋል፡

ይህም የገቢ አቅምን ለመጨመር፤ኢኮኖሚያዊ ፍትሃዊነትን እንዲሁም የኑሮ ጥራትን ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል፡፡

ወደፊትም ማህበረሰቡን በብዙ መልኩ የሚጠቅም በመሆኑ መንግስት የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026