🔇Unmute
ጅግጅጋ ፤መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰቡን የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን በጥናት እና ምርምር እያገዘ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ሙሳ መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሶማሌ ክልል ውኃ ቢሮ አዘጋጅነት ዓለም አቀፍ የውኃ ቀንን ምክንያት በማድረግ የምክክር መድረክ በዩኒቨርሲቲው ተካሂዷል።

የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ሙሳ መሐመድ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ውኃ ለማንኛውም ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ወሳኝ ነው።
በመሆኑም በዚህ ዘርፍ የሚከናወኑ ሥራዎች በተለይ እንደ ሶማሌ ክልል ላሉ ቆላማ አካባቢዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲውም ይህንን ታሳቢ በማድረግ ከክልሉ ውኃ ቢሮና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ እያከናወናቸው ካሉ ተግባራት መካከል ተማሪዎችን በገጸ-ምድርና በከርስ-ምድር ውኃ ልማት ዘርፎች ማሰልጠንና ማስመረቅ አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
በተጨማሪም በውኃ ሀብት ልማት ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥናት እና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የውኃ እጥረት ያለባቸውን አካባቢዎችን በተለያዩ መንገዶች የመደገፍ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የሶማሌ ክልል ውኃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ መሐመድ በበኩላቸው፤ መንግሥት የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተደራሽነትን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የክልሉ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ሽፋን 51 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፣ በገጠርና በከተሞች ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በመድረኩ ላይ ምሁራን እና ባለድርሻ አካላት የውኃ አገልግሎት ተቋማትን የማስተዳደር አቅም ማጎልበት እንዲሁም ቴክኖሎጂን በመጠቀም የውኃ ተጠቃሚነትን ማስፋፋት ትኩረት ሊያገኙ ይገባል ብለዋል።
የውኃ ፕሮጀክቶች በቋሚነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል የጥገናና የክትትል አቅምን ማሳደግ እና ኅብረተሰቡ በዝናብ ወቅት ውኃን የመቆጠብና የመጠቀም ግንዛቤው እንዲጎለብት መስራት ከባለድርሻ አከላት የሚጠበቅ መሆኑ ተመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026