🔇Unmute
ጅግጅጋ ፤መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰቡን የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን በጥናት እና ምርምር እያገዘ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ሙሳ መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሶማሌ ክልል ውኃ ቢሮ አዘጋጅነት ዓለም አቀፍ የውኃ ቀንን ምክንያት በማድረግ የምክክር መድረክ በዩኒቨርሲቲው ተካሂዷል።

የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ሙሳ መሐመድ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ውኃ ለማንኛውም ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ወሳኝ ነው።
በመሆኑም በዚህ ዘርፍ የሚከናወኑ ሥራዎች በተለይ እንደ ሶማሌ ክልል ላሉ ቆላማ አካባቢዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲውም ይህንን ታሳቢ በማድረግ ከክልሉ ውኃ ቢሮና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ እያከናወናቸው ካሉ ተግባራት መካከል ተማሪዎችን በገጸ-ምድርና በከርስ-ምድር ውኃ ልማት ዘርፎች ማሰልጠንና ማስመረቅ አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
በተጨማሪም በውኃ ሀብት ልማት ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥናት እና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የውኃ እጥረት ያለባቸውን አካባቢዎችን በተለያዩ መንገዶች የመደገፍ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የሶማሌ ክልል ውኃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ መሐመድ በበኩላቸው፤ መንግሥት የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተደራሽነትን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የክልሉ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ሽፋን 51 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፣ በገጠርና በከተሞች ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በመድረኩ ላይ ምሁራን እና ባለድርሻ አካላት የውኃ አገልግሎት ተቋማትን የማስተዳደር አቅም ማጎልበት እንዲሁም ቴክኖሎጂን በመጠቀም የውኃ ተጠቃሚነትን ማስፋፋት ትኩረት ሊያገኙ ይገባል ብለዋል።
የውኃ ፕሮጀክቶች በቋሚነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል የጥገናና የክትትል አቅምን ማሳደግ እና ኅብረተሰቡ በዝናብ ወቅት ውኃን የመቆጠብና የመጠቀም ግንዛቤው እንዲጎለብት መስራት ከባለድርሻ አከላት የሚጠበቅ መሆኑ ተመልክቷል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026