የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የነዳጅ ብክነትን ለመቀነስ ምን ዓይነት ብልኀት መጠቀም ይመከራል?

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ከሰሞኑ የተከሰተውን የመካከለኛው ምሥራቅ ግጭት ተከትሎ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገራት ምርቱን እንደወትሮው እያገኙ አለመሆኑ ይታወቃል፤ ይህም ቀደም ሲል ያስገቡትን በቁጠባ እንዲጠቀሙ እንዳስገደዳቸው ይገለጻል።

ነገሮች ወደነበሩበት እስኪመለሱ ድረስም ሀገራት፤ በአንድ በኩል የአስቸኳይ ጊዜ ርምጃዎችን እየወስዱ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የረጅም ጊዜ ስትራቴጂዎቻቸውን በመከለስ ዘላቂ መፍትሔ እያማተሩ ነው።

ስለዚህም ህብረተሰቡ ነዳጅን በቁጠባና ብክነትን በሚቀንስ መልኩ እንዲጠቀም ከሚጠቅሙ ተግብራት መካከል የሚከተሉት ተጠቃሽ ናቸው፦

• በሕዝብ ትራንስፖርት የመጠቀም ልምድን ማዳበር ለአብነትም ባቡርን፣

አውቶቡስን እና ሌሎች የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎቶችን መጠቀም፤

• ከነዳጅ ይልቅ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን የመጠቀም ልምድን ማስፋት፤

• በነዳጅ እና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ (Plug-in Hybrid) ተሽከርካሪዎች ነዳጅን በመተው የኤሌክትሪክ ኃይልን ብቻ እንዲጠቀሙ ማስቻል፤

• በነዳጅ የሚሠሩትን ወደ ኤሌክትሪክ እና ተፈጥሮ ጋዝ የመቀየር ሥራን ማጠናከር፤

• በከተማ ውስጥ የሚደረጉ አጫጭር ጉዞዎችን በእግርና በብስክሌት የማድረግ ባህልን ማሳደግ፤

• በነዳጅ የሚሠሩ መኪኖችን የሞተር ዘይት፣ ፊልተር እና የጎማ ዓየር ግፊት በየጊዜው ከመፈተሽ አለመቦዘን፤ ወቅታዊ የመኪና ጥገናን ማጠናከርና ኦሪጅናል መለዋወጫዎችን መጠቀም፤

• መኪና አቁሞ መጠበቅ የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲኖር ሞተሩን ማጥፋት፤

• የሞተሩን ጫና ለመቀነስ ጭነት አለማብዛት፤

• እስከ 20 ቶን የሚጭኑ የጭነት ተሽከርካሪዎች ወደ ኤሌክትሪክ፤ ከ20 ቶን በላይ የሆኑት ደግሞ ወደ ተፈጥሮ ጋዝ እና ኤሌክትሪክ እንዲቀየሩ ማድረግ፤

በሌላ በኩል የንግድና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር፤ በነዳጅ ሥርጭትና ግብይት ሂደት ላይ የሚታዩ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር በክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች የተጀመረው የተቀናጀ ዘመቻ መጠነ ሰፊ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጿል። ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት መቸገራቸውን አውስተው፤ ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስከምንመለስ ድረስ የነዳጅ አከፋፋዮች፣ ማደያዎች እና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ፣ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት በኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙ ማሳሰባቸው ይታወሳል።

#አረንጓዴ_ትራንስፖርት #ነዳጅን_መቆጠብ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026