🔇Unmute
ጅማ፤ መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡ ስኬታማ የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ምሁራን ድርሻቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተመለከተ።
በጅማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን እየተሳተፉ ነው።

በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሁሉን አቀፍ የልማት ስኬቶች ተመዝግበዋል።
በተለይም በግብርና፣ በትምህርት እና በጤና ዘርፎች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት በተሻለ መልኩ ያሳደጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ ከትምህርት ጥራት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የቡዑረ ቦሩ የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶች በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በስፋት መገንባታቸውን አስታውሰዋል።
ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመቅረፍም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋፋትና የዲጂታል አገልግሎትን ተደራሽ የማድረግ ስራ ውጤታማ እንደሆነ አመልክተዋል።
እነዚህ የተመዘገቡ ስኬታማ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ምሁራን በጥናትና ምርምር የማገዝ ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በመድረኩ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የክልሉ መንግሥት ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ(ዶ/ር)፤ በክልሉ ሲተገበሩ የቆዩ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተተገበሩ አዳዲስ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጉዞ ያጠናከሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በ2010 ዓ.ም በ1 ነጥብ 9 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ ብቻ ይለማ የነበረው የስንዴ ምርት፣ አሁን ላይ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት ወደ 6 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር ማሳደግ መቻሉን ለአብነት አንስተዋል።
ይህ ስኬት የተገኘውም በዓመት ሁለት ጊዜና ከዚያ በላይ ማምረት በመቻሉ መሆኑን ገልጸው፤ ለመጪው ትውልድ የተሻለ ኢኮኖሚ ለማውረስ ሁሉም በጋራ መረባረብ አለበት ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026