የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዘንድሮው የመኸር እርሻ 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዷል 

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦በዘንድሮው የመኸር እርሻ 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን መታቀዱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር የ2018/19 የመኸርና የበልግ ወቅት የሰብል ልማት ንቅናቄን በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በመግለጫቸው እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የመኸር፣ የበልግና የበጋ መስኖ ልማት ስራዎች በተቀናጀ መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ።

"ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነት በሀገር ደረጃ ማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ የሰብል ምርትን በመሬት ሽፋንና በምርታማነት ማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለግብርና ስራ ምቹ የሆነ የሰብል ልማት ስነ-ምህዳር ያላት በመሆኑ፣ በክልሎች የሚገኙ ጸጋዎችን በመለየት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።

ከ2011/12 የምርት ዘመን ጀምሮ በመኸር፣ በበልግ እንዲሁም በስንዴ ልማትና በሌሎች ምርቶች የሚታረስ መሬት በመጠንም ሆነ ከሄክታር የሚገኘው ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡

ለአብነትም በ2011 ዓ.ም በ3 ሺህ 500 ሄክታር መሬት ላይ የተጀመረው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ዘንድሮ 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መድረሱን ገልጸዋል፡፡

በዚህም መጀመሪያ ላይ ይገኝ የነበረው 100 ሺህ ኩንታል ምርት፣ በዘንድሮው ዓመት ወደ 175 ሚሊዮን ኩንታል ከፍ ማለቱን ተናግረዋል፡፡

የመኸር ስንዴ ልማት በ2011 ዓ.ም ከነበረው 1 ነጥብ 75 ሚሊዮን ሄክታር ሽፋን በአሁኑ ወቅት ወደ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ማደጉን ጠቅሰዋል፡፡

በመኸር የሰብል ልማት የእርሻ መሬትና በሄክታር የሚገኝ ምርታማነት በየዓመቱ እያሳየ የመጣውን ጭማሪ ተከትሎ ለቀጣዩ የ2018/19 የመኸር ወቅት 21 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ግብ መቀመጡን ተናግረዋል፡፡

ለበልግ እርሻ 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እስካሁን 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ለተመዘገበው ስኬት የአመራሩ ቁርጠኝነት ወሳኝ ሚና መጫወቱንም አንስተዋል፡፡

የኩታ ገጠም እርሻ መስፋፋት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን ማሽነሪዎች አቅርቦት ማደግ፣ የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር አቅርቦት መሻሻል ለግብርናው ዘርፍ እድገት ተጠቃሽ ምክንያቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026