የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለህገ-ወጥ ግብይት ሊውል የነበረ ከ80 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተያዘ

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባምንጭ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለህገ-ወጥ ግብይት ሊውል የነበረ ከ80 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ሲያዝ ስምንት ማደያዎችም ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መታሸጋቸውን የክልሉ የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።

የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በኢትዮጵያ የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን የመፍትሄ አቅጣጫዎች በተመለከተ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል።

የችግሩን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገና መፍትሄዎችን ያገናዘበ አሰራር መከተልና መፍትሄውን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን ከተቀመጠው አሰራር ውጭ ግብይት እንዳይኖር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ ነው።

በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የነዳጅ ስርጭትና አጠቃቀም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ሲሆን ከዚህ አሰራር ውጭ ህገ ወጥ ተግባር ላይ የተጠናከረ ቁጥጥርና ክትትል በመደረግ ላይ ይገኛል።

ከዚሁ ጋር በተገናኘ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ የሰጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን፤ አሰራሩን ተግባራዊ የማድረግና ቁጥጥሩን የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት ለህገ-ወጥ ግብይት ሊውል የነበረ ከ88 ሺህ 24 ሊትር በላይ ናፍጣና ቤንዚን ከወንጀሉ ተጠርጣሪ 39 ግለሰቦች ጋር መያዙን ጠቅሰዋል።

በተደረገው ክትትልና ቁጥጥር ስምንት ማደያዎችም ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መታሸጋቸውን ገልጸው ከህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትና ስርጭት ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ እየሰጠ ያለው ጥቆማ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጣው የነዳጅ ቁጠባ መመሪያ በክልሉ ባሉ ማደያዎች ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በከፍተኛ የመንግስት ድጎማ እየመጣ ያለው ነዳጅ በፍትሃዊ መንገድ እንዲሰራጭ የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026