የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለህገ-ወጥ ግብይት ሊውል የነበረ ከ80 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተያዘ

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባምንጭ፤ መጋቢት 24/2018(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለህገ-ወጥ ግብይት ሊውል የነበረ ከ80 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ሲያዝ ስምንት ማደያዎችም ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መታሸጋቸውን የክልሉ የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።

የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በኢትዮጵያ የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን የመፍትሄ አቅጣጫዎች በተመለከተ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል።

የችግሩን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገና መፍትሄዎችን ያገናዘበ አሰራር መከተልና መፍትሄውን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን ከተቀመጠው አሰራር ውጭ ግብይት እንዳይኖር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ ነው።

በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የነዳጅ ስርጭትና አጠቃቀም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ሲሆን ከዚህ አሰራር ውጭ ህገ ወጥ ተግባር ላይ የተጠናከረ ቁጥጥርና ክትትል በመደረግ ላይ ይገኛል።

ከዚሁ ጋር በተገናኘ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ የሰጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን፤ አሰራሩን ተግባራዊ የማድረግና ቁጥጥሩን የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት ለህገ-ወጥ ግብይት ሊውል የነበረ ከ88 ሺህ 24 ሊትር በላይ ናፍጣና ቤንዚን ከወንጀሉ ተጠርጣሪ 39 ግለሰቦች ጋር መያዙን ጠቅሰዋል።

በተደረገው ክትትልና ቁጥጥር ስምንት ማደያዎችም ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መታሸጋቸውን ገልጸው ከህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትና ስርጭት ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ እየሰጠ ያለው ጥቆማ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጣው የነዳጅ ቁጠባ መመሪያ በክልሉ ባሉ ማደያዎች ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በከፍተኛ የመንግስት ድጎማ እየመጣ ያለው ነዳጅ በፍትሃዊ መንገድ እንዲሰራጭ የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026