የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

ቋሚ ኮሚቴው በጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የአስረጂ መድረክ አካሂዷል።

በዚሁ ወቅት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ፤ በረቂቅ አዋጁ ሥርዓት ክፍተትን የሚያርሙ ድንጋጌዎች እንደተካተቱ ገልጸዋል።


የኢትዮጵያን አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የንግድ ተወዳዳሪነትን የሚያሳልጥ ዓለም አቀፍና አዳዲስ የጉምሩክ አገልግሎት ማቀላጠፊያ ድንጋጌዎች መካተታቸውን ተናግረዋል።

በዚህም የአዋጁ ማሻሻያ የኮሚሽኑን ተግባርና ኃላፊነት በተቀላጠፈ የአሰራር ሥርዓት በመምራት ውስብስብ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን መግታት በሚያስችል መልኩ እየተዘጋጀ ነው ብለዋል።

የምክር ቤቱ አባላትና የሕግ ሙያተኞችም፤ በረቂቅ አዋጅ ላይ ምላሽና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮችን በማስመልከት ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች አስተያየትና ጥያቄ አቅርበዋል።

በረቀቂ አዋጁ ላይ የገቢ ምርቶችን የቆይታ ጊዜ በማስመልከት ከዚህ ቀደም ከነበረው አንፃር ሲታይ ከፍ እንዲል መደረጉን በማስመልከት ምላሽና ማብራሪያ ጠይቀዋል።


የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በምላሽና ማብራሪያቸው፤ የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ከዚህ ቀደም የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን ለማረም ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

በዚህም በረቂቅ አዋጁ ውስብስብ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን መከላከል የሚያስችሉ ወሳኝ ድንጋጌዎችን በማካተት እየተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ የኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የሚያቀላጥፍ አስቻይ የጉምሩክ አገልግሎት አሰጣጥ ተቋማዊ የሪፎርም አካል መሆኑን ገልጸዋል።


በተጨማሪም በዕቃዎች የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት የሚጠናቀቅበት ጊዜ፣ የዋጋ አወሳሰን፣ በይግባኝ አቀራረብ፣ በጉምሩክ ጥሰት የሚወረሱ ንብረቶች አስተዳደር፣ የዋስትና አያያዝ ላይ የተደረጉ ጉልህ ማሻሻያዎች ላይም ማብራርያ ሰጥተዋል።

በገንዘብ ሚኒስቴር የታክስ ጉዳዮች አማካሪ ዋሲሁን አባተ፤ በረቀቂ አዋጁ ላይ የጉምሩክ ሥነ-ስርዓትን ያሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ወሳኝ ድንጋጌዎች መካተታቸውን አስረድተዋል።

በዚህም በረቂቅ አዋጁ ላይ የጉምሩክ አገልግሎቶችን የሚያቀላጥፉ አመቺና አዳዲስ ዓለም አቀፍ የአሰራር ሥርዓት መርሆችና ድንጋጌዎች እንደተካተቱ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025