🔇Unmute
ገንዳውኃ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውኃ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ950 ሊትር በላይ ነዳጅ መያዙን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ሀይሌ ብርሃኑ 900 ሊትር ናፍጣ እና 56 ሊትር ቤንዚን በግለሰብ ቤት ከተደበቀበት ለመያዝ መቻሉን ገልጸዋል።

በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረው ነዳጅ ሊያዝ የቻለው የጸጥታ አካላት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻና ጥብቅ ክትትል መሆኑንም ተናግረዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ ነዳጁ በህገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘው በከተማው ቀበሌ 03 ልዩ ቦታው ቀጠና 08 በተባለ አካባቢ ነው።

በቀጣይም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጫና የሚፈጥሩ መሰል ህገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ህገ ወጥ ተግባር ተፈጽሞ ሲያይ ለጸጥታ አካላት ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ትብብር በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025