የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በዞኑ ሞዴል አርሶ አደሮችን ወደ ኢንቨስትመንት የማሻገር ስራ እየተሰራ ነዉ

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሚያዚያ 10/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ሞዴል አርሶ አደሮችን እና በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተዉ ስኬታማ የሆኑ ማህበራትን ወደ ኢንቨስትመንት የማሸጋገር ስራ እየተካሔደ ነዉ።

በጅማ ዞን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሰፋፋ የመጣዉን የመሠረተ ልማት ግንባታ ተከትሎ በኢንቨስትመንት የሚሰማሩ ባለሀብቶች ቁጥር እየጨመረ መሆኑም ተገልጿል።

በተያዘው ዓመትም 1 ሺህ 680 ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ ማስገባቱን የዞኑ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ፅህፈት ቤት አመልክቷል።

የፅህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ዘሊካ ቡላ ለኢዜአ እንደተናገሩት ፤በተያዘው ዓመት በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ 20 ማህበራት፣ 39 የህብረት ስራ ማህበራትን ጨምሮ በድምሩ 1 ሺህ 680 ፕሮጀክቶች ወደ ኢንቨስትመንት ገብተዋል።

ወደ ኢንቨስትመንት ከገቡት 1 ሺህ 680 ፕሮጀክቶች ውስጥ ደግሞ 1 ሺህ 621 የሚሆኑት ሞዴል አርሶ አደሮች መሆናቸውን ነው የገለጹት፤

ወደ ኢንቨስትመንት የገቡት ባለሃብቶችም 4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ መሆናቸዉንም ነው ያመለከቱት።

ለኢንቨስትመንት ስራዉ 7 ሺህ 578 ሄክታር መሬት መሰጠቱን የገለፁት ስራ አስኪያጇ ለፕሮጀክቶቹ ተግባራዊነት ጠንካራ የሆነ ክትትልና ደጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በዞኑ ለኢንቨስትመንት መሬት ተረክበዉ ወደ ስራ መግባት ያልቻሉትን በመለየትም የፋይናንስ እና የሊዝ ማሽን አቅርቦት ችግር ያለባቸውን በመለየት ከባንክ ብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅትም ሙያዊ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን አመልክተው አስፈላጊዉ ድጋፍ ተደርጎላቸዉ ወደ ስራ መግባት ያልቻሉ ባለሀብቶች ፍቃዳቸዉ የሚሰረዝበት አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግም ነው የጠቀሱት።

በሌላ በኩል በተቋም ደረጃ አገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን እና የማቀላጠፍ ስራ ትኩረት የተሰጠዉ ሲሆን ፣ ከዚህ ቀደም የነበሩ የተንዛዙ አሰራሮችን በማስቀረት የተሻለ አገልግሎት እየተሰጠ ነዉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026