🔇Unmute
ሸገር፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ ባለፉት ሦስት ዓመታት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለኢንቨስትመንት ሥራዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን የከተማዋ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኃላፊ መኮንን አምባው ገለጹ።
ኃላፊው ለኢዜአ እንዳሉት፤ መሶብ በሁሉም ዘርፎች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ማነቆዎችንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ለኢንቨስትመንት ሥራዎች መስፋፋት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
ይህንን የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይበልጥ ለማጠናከር የከተማው አስተዳደር በከተማ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በክፍለ ከተሞችም ጭምር ተግባራዊ ለማድረግ እየሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
አገልግሎቱ ተገልጋዮች የሚፈልጉትን አገልግሎት በአንድ ቦታ በፍትሐዊነት እንዲያገኙ እያደረገ በመሆኑ የከተማዋን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይበልጥ ቀልጣፋ እያደረገው ነው ብለዋል።

ይህንን ሥራ ይበልጥ ለማጠናከር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ወደ ተንቀሳቃሽነት በመለወጥ ዘርፉን በቅርበት ለማገልገል ሰፊ ሥራ መጀመሩንም አስታውቀዋል።
በከተማዋ 32 የተለያዩ ሴክተሮችን በአንድ ማዕከል በማገናኘት ማኅበረሰቡ ቀልጣፋና ግልጽነት ያለው አገልግሎት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በማዕከሉ 159 የሥራ ዓይነቶች አገልግሎት እየተሰጠባቸው መሆኑን ገልጸው፤ ከመደበኛ የሥራ ቀናት በተጨማሪ በምሳ ሠዓትና በእሁድ ቀናትም አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሸገር ከተማ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለተገልጋዮች ምቹ ሁኔታን የፈጠረና የአገልግሎት አሰጣጥ ዕርካታን ያረጋገጠ መሆኑን የከተማዋ ተገልጋዮች ገልጸዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026