🔇Unmute
ቦንጋ ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ የተከናወኑት ተግባራትህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ መሆናቸውንየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
በክልሉ የመንግስትና የፓርቲ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ህብረተሰቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ የተከናወኑት ተግባራት ለህዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ናቸው።
በመሰረተ ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በግብርና፣ በስራ እድል ፈጠራ ፣ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል።
በክልሉ የተመዘገቡ ልማቶች አበረታች ቢሆኑም ከክልሉ የመልማት አቅም አንፃር ገና ሰፊ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ ይበልጥ መትጋት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለዚህም የክልሉን አመራሮችና ሰራተኞች እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በማቀናጀት ተከታታይነት ያለው ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባም አክለዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በመንግስትም ሆነ በፓርቲ የተመዘገቡ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል ያሉት ደግሞ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።

በተለይም አመራሩ ስራን በመገምገምና በቅንጅት በመስራት እንዲሁም ህብረተሰቡን በማስተባበር የመጡ ውጤቶችን ማስቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026