🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በኢኮኖሚ ዘርፍ ላይ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፀደይ ስብሰባ ጎን ለጎን በዋሽንግተን ዲሲ ከፈረንሳይ ግምጃ ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበርም ተመላክቷል።

ፈረንሳይ የመንግሥታት አበዳሪዎች ኮሚቴን በሊቀ መንበርነት በመራችበት ወቅት በኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ላይ ላበረከተችው አስተዋጽኦም ሚኒስትር አህመድ ሽዴ አመስግነዋል።
ሁለቱ ሀገራት በኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት ላይ በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
ይህም አዳዲስ የፋይናንስ ፍሰቶችን ለማምጣትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026