🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በኢኮኖሚ ዘርፍ ላይ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፀደይ ስብሰባ ጎን ለጎን በዋሽንግተን ዲሲ ከፈረንሳይ ግምጃ ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበርም ተመላክቷል።

ፈረንሳይ የመንግሥታት አበዳሪዎች ኮሚቴን በሊቀ መንበርነት በመራችበት ወቅት በኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ላይ ላበረከተችው አስተዋጽኦም ሚኒስትር አህመድ ሽዴ አመስግነዋል።
ሁለቱ ሀገራት በኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት ላይ በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
ይህም አዳዲስ የፋይናንስ ፍሰቶችን ለማምጣትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026