የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ ግዙፍ የግብርና ኢንቨስትመንት አቅም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ ነው

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያላት ሰፊ የግብርና ሃብት አቅም በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት እያሳደገው መሆኑን በኢትዮጵያ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት የሕንድ ባለሃብት ጋጀንድራ ሲንገህ ማንፑራ ገለጹ።

ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ተግባራዊ ያደረገቻቸው የሪፎርም ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እያመጡ ነው።

በተለይም በምግብ ራስን ለመቻልና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ተቀይሰው ሥራ ላይ የዋሉ እንደ የስንዴ ልማት ዓይነት ኢኒሼቲቮች ተጠቃሽ ናቸው።

የስንዴ ምርት የሀገር ውስጥ ፍጆታን በመሸፈን ወደ ውጭ መላክ መጀመሩ ኢኒሼቲቩ ፍሬያማ መሆኑን አመላካች ነው።

በግብርና ኢንቨስትመንት በኩልም ባለኃብቶችን የሚያበረታቱ ምቹ ሁኔታዎች ከመፍጠር ባለፈ በዘርፉ ያላት እምቅ አቅም የሀገር ውስጥና የውጭ ባለኃብቶችን በከፍተኛ ሁኔታ እየሳበ ነው።

የሕንድ ባለሀብት ጋጀንድራ ሲንገህ ማንፑራ፤ በደቡብ አፍሪካ፣ ታንዛኒያ፣ ኬኒያ፣ ዛምቢያና በሌሎች ሀገራት የኢንቨስትመንት ዳሰሳ ጉብኝት ማድረጋቸውን አስታውሰዋል።

በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝትም ሀገሪቷን ለግብርና ኢንቨስትመንት ተመራጭ በማድረግ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ተሰማርተው እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በተለይም የአቮካዶ ምርትን በማሳደግ ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች ለማቅረብ በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም በሙዝ፣ በእንጆሪ፣ በቅመማ ቅመም እና በተለያዩ የግብርና ዘርፎች ኢንቨስትመንታቸውን ለማስፋት በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

አሁን ላይ በ500 ሺህ ዶላር መነሻ ካፒታል እየሰሩ መሆኑን የገለጹት ባለሀብቱ፤ በቀጣይም ኢንቨስትመንታቸውን በሦስት እጥፍ የማሳደግ ዕቅድ እንዳላቸው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የግብርና ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ የድጋፍና የክትትል ሥርዓት እንዲሁም አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል።

መንግሥት ከመሬት አቅርቦት በተጨማሪ እንደ መንገድ፣ ኤሌክትሪክና የውሃ አቅርቦት ያሉ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት የአልሚዎችን አቅም እያጠናከረ መሆኑንም ተናግረዋል።

ይህም የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ምቹ ሁኔታ፣ ሀገሪቷን የዓለም አቀፍ ገበያ ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል አቅም እንዳላት ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026