🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኦሮሞ ምርምር ማህበር የኦሮሞን ህዝብ ታሪክ ለመሰነድና ትውልድን በእውቀት ለመቅረጽ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገለጸ።
ማህበሩ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 2ኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ መካሄድ ጀምሯል።

የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር በቀለ ጉተማ፤ የኦሮሞ ምርምር ማህበር የኦሮሞን ህዝብ ታሪክ፣ ባህል፣ ቋንቋ እና የገዳ ስርዓትን በጥናትና ምርምር በመፈተሽ ለትውልድ ለማስተላለፍ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የኦሮሞን ጥልቅ ዕውቀት መመርመርና ማሳወቅ፣ የህዝቡን ትናንት አጥንቶ ማስገንዘብ፣ ዛሬን መፈተሽና መተቸት፣ እንዲሁም የወደፊቱን እጣ ፈንታ መተንበይና አቅጣጫ መጠቆም ከማህበሩ ተልዕኮዎች ዋነኞች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ማህበሩ ትውልዱን በማስተማርና የወደፊት ጉዞውን ለማቅናት የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎችንና መድረኮችን በማዘጋጀት፤ ባህልና እሴቶችን ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ ምሁራንን በማሳተፍ ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ማህበሩ ከተመሰረተ ጀምሮ የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በማዘጋጀት ምሁራን በኦሮሞ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ እንዲለዋወጡ ማድረጉን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምርምር እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በባህላዊና ታሪካዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ አራት መጻህፍት በተለያዩ ቋንቋዎች አሳትሞ ማሰራጨቱን አስታውሰዋል።
በአሁኑ ወቅትም በስድስት የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑንና በቅርቡ ለህትመት እንደሚበቁም ጠቁመዋል።

የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ሰለሞን ማሾ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በኦሮሞ ባህልና እሴቶች ላይ በንቃት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ ከሚሰሩ ማናቸውም ተቋማት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝና ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ መሰል የምርምር ተቋማት የህዝብን ታሪክ፣ ባህልና ማንነት ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ያላቸው ፋይዳ የላቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ይደረግባቸዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026