የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያን የፈጠራ ባለቤትነት መብት ጥበቃ ከዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር የሚያጣጥም የሕግ ማሻሻያ እየተደረገ ነው

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን የፈጠራ ንብረት ባለቤትነት መብት ጥበቃ ከአህጉራዊና ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር የሚያጣጥም አዳዲስ የሕግ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ገለጸ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ የሚሹ ሃብቶች ሕጋዊ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ለሚጠይቁ ዜጎች አገልግሎት እየተሰጠ ነው።

የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነት ጥበቃን ለማዘመንም ዘመናዊ የአሰራርና የሕግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ለአብነትም ረጅም ዘመናትን ያስቆጠሩ ተቋማዊ ሕግጋትን በማሻሻል ዘመኑን የዋጀ የአሰራር ሥርዓት እንዲፈጠር መደረጉን አንስተዋል።

የአሰራርና የሕግ ማዕቀፎቹም የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነት ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገቡ ሃብቶችን ማስጠበቅ እያስቻሉ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት ባለቤትነት መብት ጥበቃ ከዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር የሚያጣጥም አዳዲስ የሕግ ማሻሻያ እየተደረገ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል።

የባለስልጣኑ ዘመናዊ የአሰራርና የሕግ ማሻሻያም የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነትን በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የሙያተኞችን የመፈጸም አቅም በማጎልበት የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን የሚያረጋግጥ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዓመታት በፊት በተለያዩ ዘርፎች ይሰጥ የነበረውን ከ3ሺህ የማይበልጥ የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነት ጥበቃ አሁን ላይ በዓመት ወደ 9ሺህ ምዝገባ ማድረግ የሚቻልበት አቅም መፈጠሩን ጠቅሰዋል።


በኢትዮ-አሊያንስ አድቮኬሲ የአዕምሯዊ ንብረትና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ደሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ የሕግ ማሻሻያዎች አሰራርን በማዘመን ገንቢ ሚና አላቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ውጤታማነትን ለማረጋገጥም የዓለም አቀፍ ተቋማትን ትብብር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

በቀጣይም የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት ሃብቶች ጥበቃ የበለጠ ለማጠናከር ሕግጋትን ማዘመንና የሙያተኞችን ብቃት ማጎልበት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026