የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያን የፈጠራ ባለቤትነት መብት ጥበቃ ከዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር የሚያጣጥም የሕግ ማሻሻያ እየተደረገ ነው

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን የፈጠራ ንብረት ባለቤትነት መብት ጥበቃ ከአህጉራዊና ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር የሚያጣጥም አዳዲስ የሕግ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ገለጸ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ የሚሹ ሃብቶች ሕጋዊ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ለሚጠይቁ ዜጎች አገልግሎት እየተሰጠ ነው።

የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነት ጥበቃን ለማዘመንም ዘመናዊ የአሰራርና የሕግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ለአብነትም ረጅም ዘመናትን ያስቆጠሩ ተቋማዊ ሕግጋትን በማሻሻል ዘመኑን የዋጀ የአሰራር ሥርዓት እንዲፈጠር መደረጉን አንስተዋል።

የአሰራርና የሕግ ማዕቀፎቹም የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነት ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገቡ ሃብቶችን ማስጠበቅ እያስቻሉ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት ባለቤትነት መብት ጥበቃ ከዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር የሚያጣጥም አዳዲስ የሕግ ማሻሻያ እየተደረገ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል።

የባለስልጣኑ ዘመናዊ የአሰራርና የሕግ ማሻሻያም የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነትን በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የሙያተኞችን የመፈጸም አቅም በማጎልበት የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን የሚያረጋግጥ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዓመታት በፊት በተለያዩ ዘርፎች ይሰጥ የነበረውን ከ3ሺህ የማይበልጥ የአዕምሯዊ ንብረት መብትና ባለቤትነት ጥበቃ አሁን ላይ በዓመት ወደ 9ሺህ ምዝገባ ማድረግ የሚቻልበት አቅም መፈጠሩን ጠቅሰዋል።


በኢትዮ-አሊያንስ አድቮኬሲ የአዕምሯዊ ንብረትና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ደሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ የሕግ ማሻሻያዎች አሰራርን በማዘመን ገንቢ ሚና አላቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት ጥበቃ ውጤታማነትን ለማረጋገጥም የዓለም አቀፍ ተቋማትን ትብብር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

በቀጣይም የኢትዮጵያን የአዕምሯዊ ንብረት ሃብቶች ጥበቃ የበለጠ ለማጠናከር ሕግጋትን ማዘመንና የሙያተኞችን ብቃት ማጎልበት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026