የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአፈር ለምነትን በዘላቂነት የሚጠብቁ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮች እየተጠናከሩ ነው

May 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ግንቦት 15/2018(ኢዜአ)፦ የአፈር ለምነትን በዘላቂነት የሚጠብቁ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን በመተግበር ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ።

ኢንስቲትዩቱ በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል አዲስ በአፈርና ውሃ ላይ ጥናትና ምርምር ለማድረግ የሚያግዝ ላብራቶሪ ስራ አስጀምሯል።


የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ንጉሤ ደቻሳ (ፕ/ር) እንደገለጹት፤ የአፈር ለምነትን መጠበቅ ለምርትና ምርታማነት እድገት መሰረታዊ በመሆኑ፣ የአፈር ለምነትን የሚቀንሱ ችግሮችን በሳይንሳዊ ዘዴ መለየትና የላብራቶሪ ማዕከላትን ማጠናከር አስፈልጓል።

በአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዛሬ ተመርቆ ስራ የጀመረው የአፈር እና ውሃ ላብራቶሪም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።


የላብራቶሪው ዋና ዓላማም የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማድረግና የግብርናውን ዘርፍ ማሳደግ እንደሆነ አንስተዋል።

የአምቦ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ጀማል ቶላ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ማዕከሉ ባለፉት ዓመታት ከአካባቢው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ለእጽዋት ጥበቃ የሚውሉ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶችን ሲያቀርብ መቆየቱን ተናግረዋል።


የምርት መጠንን ለመጨመር የሰብል ልማትን የሚደግፉ ሰፋፊ የግብርና ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ይህም የአካባቢውን አርሶ አደሮች ከመደገፍ ባለፈ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እንዲከናወኑ ማድረጉን ተናግረዋል።

ማዕከሉ ግብርናን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችንና የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል።


የአምቦ ወረዳ አርሶ አደር ወይዘሮ እሸቱዋ ሚደቅሳ በበኩላቸው፤ ከግብርና ማዕከሉ ባገኙት ስልጠና በመታገዝ የተሻሻለ የበቆሎ ዝርያ ወስደው በመዝራታቸው፣ ምርታቸው ከበፊቱ እጥፍ መጨመሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026