🔇Unmute
ሆሳዕና፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይ በሁሉም የልማት ሥራዎች ላይ በድጋሚ ለማረጋገጥ መዘጋጀታቸውን ገለጹ።
በሆሳዕና ከተማ የሴች ዱና ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ እንዳሻሽ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይበጀናል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ሰጥተዋል።
በምርጫ ወቅት ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይም በሀገር ልማት ላይ በመድገም የተጀመረውን ሀገራዊ ልማት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።
በከተማው በሊች አምባ ቀበሌ የሚኖሩት አቶ ሀብቴ አስራት በሰጡት አስተያየት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይበጀኛል ላሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
በምርጫው ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይም በልማት እንደሚደግሙት ገልፀዋል።
በሆሳዕና ከተማ ሄጦ ቀበሌ ነዋሪዋ ዓለምፀሐይ ደስታ፤ በጠቅላላ ምርጫው በመሳተፍ ድምጻቸውን ለሚፈልጉት ፓርቲ በመስጠት ታሪካዊ አሻራቸውን ማሳረፋቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይም የልማት እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለፈለጉት ፓርቲ ድምጻቸውን በመስጠት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እንደተወጡ የገለጹት ደግሞ በከተማው የአራዳ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ደበበ ባሻ ናቸው።
በቀጣይም ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ልማት መጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026