የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በሁሉም የልማት መስኮች ለመድገም ተዘጋጅተዋል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦የሆሳዕና ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይ በሁሉም የልማት ሥራዎች ላይ በድጋሚ ለማረጋገጥ መዘጋጀታቸውን ገለጹ።

በሆሳዕና ከተማ የሴች ዱና ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ እንዳሻሽ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይበጀናል ለሚሉት ፓርቲ ድምፅ ሰጥተዋል።

በምርጫ ወቅት ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይም በሀገር ልማት ላይ በመድገም የተጀመረውን ሀገራዊ ልማት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

በከተማው በሊች አምባ ቀበሌ የሚኖሩት አቶ ሀብቴ አስራት በሰጡት አስተያየት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመሳተፍ ይበጀኛል ላሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

በምርጫው ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይም በልማት እንደሚደግሙት ገልፀዋል።

በሆሳዕና ከተማ ሄጦ ቀበሌ ነዋሪዋ ዓለምፀሐይ ደስታ፤ በጠቅላላ ምርጫው በመሳተፍ ድምጻቸውን ለሚፈልጉት ፓርቲ በመስጠት ታሪካዊ አሻራቸውን ማሳረፋቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይም የልማት እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለፈለጉት ፓርቲ ድምጻቸውን በመስጠት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እንደተወጡ የገለጹት ደግሞ በከተማው የአራዳ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ደበበ ባሻ ናቸው።

በቀጣይም ለሀገር ዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ልማት መጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026