🔇Unmute
አሶሳ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለቀጣናው ሀገራት የኃይል አቅርቦትን ከማረጋገጥ ባለፈ በትብብር ላይ የተመሠረተ ግንኙነትን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተመላከተ።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጣናዊ ትብብርን በማሳለጥ እና የአባይ ተፋሰስን በዘላቂነት ማልማት ላይ ያተኮረ 4ኛው አለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል።

በወቅቱም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ እንደገለፁት፤ ሕዳሴ ግድብ ለቀጣናው ሀገራት የኃይል አቅርቦትን ከማረጋገጥ ባለፈ በትብብር ላይ የተመሠረተ ግንኙነትን ለማጠናከር ያግዛል።
ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር ሀሰተኛ ክሶችንና መረጃዎችን መመከትና እውነቱን ማስረዳት ከምሁራን ይጠበቃል ብለዋል።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ለግድቡ ቅርብ ከመሆኑ የተነሳ መሰል የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማጠናከር የሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ ባለፈ ለቀጣናው ሀገራት የሚያስገኘውን ፋይዳ ማሳወቅ እንደሚገባው አመልክተዋል።

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ያሬድ ሙሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በግድቡ አካባቢው የሚኖረው ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በኮንፈረንሱ ላይ የአፍሪካና የአውሮፓ ሀገራት የዘርፉ ተመራማሪዎች በበይነ መረብ ጥናታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በግድቡ እና በአባይ ተፋሰስ ልማት ዙሪያ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026