🔇Unmute
አሶሳ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለቀጣናው ሀገራት የኃይል አቅርቦትን ከማረጋገጥ ባለፈ በትብብር ላይ የተመሠረተ ግንኙነትን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተመላከተ።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጣናዊ ትብብርን በማሳለጥ እና የአባይ ተፋሰስን በዘላቂነት ማልማት ላይ ያተኮረ 4ኛው አለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ አካሂዷል።

በወቅቱም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ እንደገለፁት፤ ሕዳሴ ግድብ ለቀጣናው ሀገራት የኃይል አቅርቦትን ከማረጋገጥ ባለፈ በትብብር ላይ የተመሠረተ ግንኙነትን ለማጠናከር ያግዛል።
ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ የምርምር ስራዎችን በማጠናከር ሀሰተኛ ክሶችንና መረጃዎችን መመከትና እውነቱን ማስረዳት ከምሁራን ይጠበቃል ብለዋል።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ለግድቡ ቅርብ ከመሆኑ የተነሳ መሰል የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማጠናከር የሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ ባለፈ ለቀጣናው ሀገራት የሚያስገኘውን ፋይዳ ማሳወቅ እንደሚገባው አመልክተዋል።

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ያሬድ ሙሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በግድቡ አካባቢው የሚኖረው ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በኮንፈረንሱ ላይ የአፍሪካና የአውሮፓ ሀገራት የዘርፉ ተመራማሪዎች በበይነ መረብ ጥናታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በግድቡ እና በአባይ ተፋሰስ ልማት ዙሪያ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026