🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከመጪው አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደውን ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ እና የቴክኖሎጂ ውድድር በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ሙሉጌታ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምርና በቴክኖሎጂ ልማት ረገድ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ይህ ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም፤ ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የጀመራቸውን የፈጠራና የምርምር ስራዎች ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥል ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ይህንን ጉባኤ በስኬት ለማካሄድ ተቋሙ በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም ከሰኔ 5 እስከ 7 2018 ዓ.ም የሚቆይ እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡
በጉባኤው ከ 16 አገራት የተወጣጡ ተመራማሪዎች እና ሌሎች አካላት የሚሳተፉ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026