የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከፊታችን አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

Jun 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፡-ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር ከመጪው አርብ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡

የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያካሂደውን ዓለም አቀፍ የምርምር ጉባኤ እና የቴክኖሎጂ ውድድር በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።


የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ሙሉጌታ (ዶ/ር) በመግለጫቸው፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምርና በቴክኖሎጂ ልማት ረገድ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።

ይህ ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም፤ ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የጀመራቸውን የፈጠራና የምርምር ስራዎች ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥል ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።

ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ይህንን ጉባኤ በስኬት ለማካሄድ ተቋሙ በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

ዓለም አቀፋዊ የምርምር ጉባዔ እና የቴክኖሎጂ ውድድርም ከሰኔ 5 እስከ 7 2018 ዓ.ም የሚቆይ እንደሚሆን አመልክተዋል፡፡

በጉባኤው ከ 16 አገራት የተወጣጡ ተመራማሪዎች እና ሌሎች አካላት የሚሳተፉ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026