የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 11 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በደን መሸፈን አስችሏል

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 11 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በደን እንዲሸፈን ማስቻሉን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ዛሬ በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሐይቅ ዳርቻ በይፋ አስጀምረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ ዓመት 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ በማስቀመጥ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊየን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ እንዳሉት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መንግሥትና ሕዝብ ተቀናጅተው ያሳኩት ታላቅ ታሪክ ነው።

ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት ሰባት ዓመታት 48 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸውን አንስተው በየዓመቱ በአማካይ 25 ሚሊየን ዜጎች በመርሃ ግብሩ መሳተፋቸውንም ተናግረዋል።

በመርሃ ግብሩ ከተተከሉት ችግኞች መካከል 60 በመቶ ያህሉ ለጥምር እርሻ የሚውሉ መሆናቸውን አንስተው 35 በመቶ ያህሉ ደግሞ የደን ዛፎች ናቸው ብለዋል።

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ትግበራ 11 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በደን እንዲሸፈን ማስቻሉንም አስረድተዋል።

የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከማሳደጉ ባለፈ የአረንጓዴነት ምጣኔን በመጨመር ወደ ውሃ አካላት የሚወርደውን የደለል መጠን እንዲቀንስ አስችሏል ነው ያሉት።

የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ በየዓመቱ ወደ ወንዞች ታጥቦ ይገባ የነበረውን የአፈር ሀብት ከ2 ቢሊየን ቶን ወደ 208 ሚሊየን ቶን ዝቅ እንዲል ማስቻሉን ተናግረዋል።

መርሃ ግብሩ የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን ማሳደግ ማስቻሉን አንስተው የመድረቅ አደጋ ተጋርጦባቸው የነበሩ የውሃ አካላት እንዲያገግሙ አድርጓልም ብለዋል።

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን መቋቋም የሚያስችል አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባትም ትልቅ አቅም እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026