🔇Unmute
ሆሳዕና፤ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የሆሳዕና ከተማን መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
ማዕከሉ በቴሌ፣በሰነድ ማረጋገጫ፣ በንግድና ገበያ ልማት፣ በገቢ፣በንግድ ባንክና በፖስታ ቤት የሚሰጡ ከ20 በላይ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማኅበረሰቡ እንደሚሰጥም ተመልክቷል።
ማዕከሉ ከወረቀት ንክኪ የጸዳ ቀልጣፋ አገልግሎት ለማኅበረሰቡ ተደራሽ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተጠቁሟል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪም የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ያስገነባውን ዘመናዊ ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከልን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
የግብይት ማዕከሉ የግብርና፣የፋብሪካና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገልጿል።

በመርሐ ግብሩ የክልል፣ የሀድያ ዞንና የሆሳዕና ከተማ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026