የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአፋር ክልል በበጀት ዓመቱ ከ8 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

Jul 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፣ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፡-በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ8 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የአፋር ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ አወል አብዱ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በክልሉ በበጀት ዓመቱ የክልሉን የገቢ ግብር አሰባሰብ ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ተሰርቷል።

ቅንጅታዊ ሥራውን ከማጠናከር ባለፈ አሰራርን የማዘመን ሥራ መሰራቱን ጠቅሰው፣ በእዚህም ውጤታማ የግብር አሰባሰብ ሥራ መከናወኑን አመልክተዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ 8 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደሥራመገባቱን አስታውሰው፣ በበጀት ዓመቱ ከ8 ቢሊዮን 524 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል ብለዋል።

በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መተግበሩ፣ የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ግንዛቤ እያደገ መምጣት እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ቁርጠኝነት ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል።

ገቢው የተገኘው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች እና ታክስ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች መሆኑንም አስረድተዋል።

እንደ አቶ አወል ገለጻ፣ ዘንድሮ የተገኘው ገቢ ባለፈው ዓመት ከተገኘው ገቢ ጋር ሲነጻጸር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አለው።

በገቢ አሰባሰብ ላይ ቅንጅታዊ አሰራርን ከመተግበር ባለፈ ህገ-ወጥነትን ለመከላከል የተሰራው ሥራ ለውጤቱ አስተዋጾ ማድረጉንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026