የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

 በክልሉ ያለውን ሰፊ የቱሪዝም ሀብት ለማልማት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ነሐሴ 8 /2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰፊ የቱሪዝም ሀብት በማልማት የታለመውን የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ስኬታማ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።

የመደመር መንግስት በቱሪዝም ዘርፍ፤ የትናንት የታሪክ ሀብትን፣ የዛሬውን ልማት እና የነገውን ብልጽግና በማቀናጀት ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ የቱሪዝም መዳረሻ የማድረግ ግብ አለው።

እሳቤው ቱሪዝምን ከቀደመው የተበታተነና የተወሰነ አካባቢ ላይ ብቻ ያተኮረ አሠራር በማውጣት፣ ከሌሎች አጠቃላይ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች (እንደ መንገድ፣ አየር መንገድ እና ሆቴሎች) ጋር ተሳስሮ የሚተገበር ጉዳይ እንደሆነ ያሳያል።

በእነዚህ አዳዲስ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች አማካኝነት የሀገርን መልካም ገጽታ ከመገንባት ባለፈ፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠርና የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን በማላቅ ውጤት እንዲያመጣ ተደርጎ ወደ ተግባር ተገብቷል።

የጋምቤላን ጨምሮ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው ልማት የሚውል ሰፊ የተፈጥሮና የሰው ሰራሽ የመስህብ ስፍራዎች ይገኛሉ።

የጋምቤላ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ኮንግ ሬት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ያለውን ሰፊ የቱሪዝም ሀብት በማልማት የታለመውን የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ስኬታማ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ።


በተለይም በክልሉ እምቅ የብዝሃ ሕይወት ሀብት ያለውን የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክን ከ"አፍሪካ ፓርክስ ኔትወርክ" ጋር በመቀናጀት ለማልማት ሰፊ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ በፓርኩ የሚገኙት የዱር እንስሳት የክረምትና የበጋ እንቅስቃሴያቸውን መሠረት ያደረገ የመዳረሻ ቦታዎችን ለማልማት በአውሮፕላን የታገዘ የቅኝት፣ የሰርቬይና የዳሰሳ ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ በባዮስፌር የተመዘገቡትን የተፈጥሮ ደኖችን ጨምሮ ሌሎች የቱሪዝም መስህቦችን ለማልማት የጥናትና ልየታ ሥራዎች መከናወናቸውን የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል።

በቢሮው የቱሪዝም መዳረሻ መሠረተ ልማት ቡድን መሪ አቶ ደርባቸው ሸዋለም በበኩላቸው፤ በክልሉ 109 የቱሪዝም መስህቦችን በጥናት በመለየት እንደየ ሀብት አቅማቸው በቅደም ተከተል ለማልማት ታቅዶ እየተሠራ ነው ብለዋል።


በተለይም ከፍተኛ የቱሪዝም አቅም ያለውን የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ ያለበትን የመሠረተ ልማት ተግዳሮት ለመፍታትና የዘርፉን ሀብት በሚፈለገው ደረጃ ጥቅም ላይ ለማዋል ከ"አፍሪካ ፓርክስ ኔትወርክ" ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በፓርኩ አቅራቢያ በሚገኘው በአሌሮ ግድብ ዘመናዊ የእንግዳ ማረፊያ ሎጆች ለመገንባት የግንባታ ግብዓቶች መቅረባቸውንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026

ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስ...

Aug 5, 2026

የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎብኝተዋል። ...

Aug 5, 2026