የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Aug 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረውን ፋይዳቨርስን በይፋ ሥራ አስጀምረናል ብለዋል።


ባለፉት ጥቂት ዓመታት የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎችን በመመዝገብ፣ ከ160 ሚሊዮን በላይ የማረጋገጫ አገልግሎቶችን በመስጠትና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ የዲጂታል ኢኮኖሚያችን የጀርባ አጥንት መሆኑን አስመስክሯል ነው ያሉት።

ዛሬ ደግሞ ይህ ስኬታችን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ተሸጋግሮ፣ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር ፋይዳቨርስ በሚል ስያሜ ራሱን የቻለ የመንግስት የልማት ድርጅት በመሆን ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል።

ይህ ውሳኔ ዲጂታል ማንነት ልክ እንደ መንገድ፣ ኃይል እና ቴሌኮሙኒኬሽን ሁሉ ለሀገራችን ተወዳዳሪነትና ዘላቂ እድገት ወሳኝ የሆነ ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ መሰረተ ልማት መሆኑን ማረጋገጫችን ነው ሲሉ ገልጸዋል።


ከሀገር አልፎ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሰረት ለቀጣናው እና ለአፍሪካ አህጉር ልምድና አቅም በማጋራት የአፍሪካ የዲጂታል ሽግግር መሪ እንድንሆን ያስችለናል። የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችን ስኬት የሚለካው በደረስንባቸው ቴክኖሎጂዎች ሳይሆን፣ ሕዝባችን እነዚህን ውጤቶች የራሱ አድርጎ ሲጠቀምባቸው እና ህይወቱ ሲለወጥ ነው።

የቴክኖሎጂ አቅርቦታችንን ጥራት በመጠበቅ፣ የዳታ ደህንነታችንን በማረጋገጥ እና የዜጎቻችንን ዲጂታል ግንዛቤ በማሳደግ የያዝነውን አቅጣጫ በበለጠ ቁርጠኝነት እንቀጥላለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 29/2018 (ኢዜአ)፦ የቤኒን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የኢፌዴሪ መሶብ አገልግሎትን ጎብኝተዋል። ...

Aug 5, 2026

ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳቨርስ በዲጂታል ሉዓላዊነታችንና በኢኮኖሚ ዕድገት ጉዟችን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስ...

Aug 5, 2026

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026