የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረትበአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው መጨመሩንየድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ተናገሩ።

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት እና ድጋፍ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እየጨመረ ይገኛል።

በተለይም በኢንዱስትሪ ማዕከልነቷ በምትታወቀው ድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ ለረጅም ጊዜ የቆሙ በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርታማነት ገብተዋል።

የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ እና ወጪ ምርቶችን በዓይነትና በብዛት በማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት እና በማስገኘት ላይ ናቸው።

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እየተደረገ በሚገኘው የተቀናጀ ድጋፍ እና ክትትል በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያሉ ችግሮች ተፈተው የማምረት አቅማቸው እንዲጨምርና ዘላቂ ዕድገት እንዲመዘገብ እያስቻለ ይገኛል ብለዋል።

በንቅናቄው የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የፋይናንስ፣ የመሬት አቅርቦት፣ የመሠረተ ልማት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ትኩረት በመሰጠቱ በዘርፉ የተከማቹ ጥያቄዎችን መፍታት እንዳስቻለ በማስታወስ።

ለአብነትም ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በፊት የአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም 42 በመቶ እንደነበር አስታውሰው፤ ዛሬ ላይ ወደ 62 ነጥብ 6 በመቶ ከፍ ማለቱንና ይኸም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ከንቅናቄው በፊት 6 አምራች ኢንዱስትሪዎች ብቻ ለውጭ ገበያ ያመርቱ እንደነበር አንስተው አሁን ላይ ወደ 13 ከፍ ብለው የውጭ ምንዛሬ እያስገኙ ይገኛሉ ብለዋል።

ከነዚህ ባሻገር ኢንዱስትሪዎቹ ከውጭ የሚገቡትን 69 ዓይነት ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬ ከማዳን በዘለለ ቀደም ሲል የፈጠሩትን የስራ ዕድል በዕጥፍ በማሳደግ ከ24 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አውስተዋል።


እንደ አቶ ሀርቢ ገለፃ ድሬደዋ የነፃ ንግድ ቀጠና እና የደረቅ ወደብና ተርሚናል ባለቤት መሆኗ እንዲሁም ለጅቡቲ ወደብ ያላት ቅርበትና በሁሉም መሠረተ ልማቶች ከጅቡቲ ጋር መተሳሰሯ በዘርፉ ተመራጭነቷን አጉልቶታል።

በኮሪደር ልማቱም ከተማዋ ዘመናዊ የስራና የመኖሪያ ከተማ መደረጓን ተከትሎ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚሰማሩ ባለሃብቶች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመሩ መሆኑን በመጥቀስ።

እነዚህን ውጤቶች በላቀ ደረጃ በማሳደግ ድሬደዋ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር የተሳካባት ቀዳሚ የብልፅግና ማሳያ ትሆናለች ብለዋል።


በቢሮው የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ክትትል ቡድን መሪ አቶ አበራ መንግስቱ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 354 ባለሃብቶች ከ59 ቢሊዮን 119 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል አስመዝግበው ወደ ስራ ገብተዋል።

በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት፣ በኮንስትራክሽን እና በግብርና ዘርፎች ለተሰማሩት የሀገርና የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ባለሃብቶቹ ወደ ማምረት ሲሻገሩ ለ11 ሺህ ሰዎች ቋሚ እና ለ7 ሺህ ሰዎች ደግሞ ጊዜያዊ የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026