የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በክልሉ የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲ አተገባበር ስልትን በተመለከተ ለተለያዩ አካላት በሃዋሳ ከተማ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና እየሰጠ ነው።


የቢሮው ሀላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ በስልጠናው ላይ እንደገለጹት፣ በክልሉ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማምረት አቅምን ለማጎልበት በተቀናጀ መንገድ ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የተዘረጉ የተለያዩ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይም በክልሉ በግብርና ምርቶች ማቀነባበር፣ በማዕድን ልማትና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የወጪና ተኪ ምርት በማምረት ተልዕኳቸውን እየተወጡ መሆኑንም ነው ያስታወቁት።

ኢንዱስትሪዎቹ ለኢኮኖሚው መነቃቃት ካላቸው ጠቀሜታ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑንም አስረድተዋል።

በቀጣይም ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በማጠናከር በርካታ ኢንዱስትሪዎችን ለመሳብና የዜጎችን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

እንደ አቶ አሻግሬ ገለጻ፤ በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ተከትሎ በተለያዩ ምክንያቶች ሥራ አቁመው የነበሩ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ወደሥራ እንዲገቡ ተደርገዋል።

በዚህም በክልሉ 44 በመቶ የነበረው የኢንዱስትሪ የማምረት አቅም ወደ 65 በመቶ ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል።

የስልጠናው ዓላማም ፖሊሲውን ወጥ በሆነና በተቀናጀ መልኩ በመተግበር ለኢንዱስትሪዎች የሚደረገውን ድጋፍ ማጠናከርና ውጤታማነትን ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል።


ከሰልጣኞች መካከል የደቡባዊ እና የማዕከላዊ ሲዳማ ዞኖች የኢኮኖሚ ልማት መምሪያ የኢንዱስትሪ ልማት ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ደበላ እና አቶ ዮሴፍ ብርሀኑ እንዳሉት ስልጠናው ዘርፉን በአግባቡ ለመደገፍና እየተመዘገበ ያለውን ውጤት ለማጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው።


በተለይ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተገኘውን ውጤት የዘርፉን ወሳኝነት ያረጋገጠ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢንዱስትሪዎችን በተቀናጀ መልኩ በመደገፍ ውጤቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንሰራለን ብለዋል።

በስልጠናው ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ደጋፊ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026