የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሀዋሳ ከተማ የኮሪደርና የሀይቅ ዳርቻ ልማት የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ እያራዘመ ነው

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ) :- የሀዋሳ ከተማ የኮሪደርና የሀይቅ ዳርቻ ልማት የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቆይታ ጊዜያቸውን እያራዘመው እንደሚገኝ የሲዳማ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ገለጸ።


በሲዳማ ክልል ታሪካዊና የተፈጥሮና የቱሪስት መስህቦችን በማልማትና በማስተዋወቅ ረገድ በተሰራው ሥራ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ3 ሚሊዮን 280 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ክልሉን መጎብኘታቸውን ቢሮው ገልጿል።


የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ አበበ ማሪሞ ለኢዜአ እንደገለፁት የቱሪስት መስህቦችን በማልማት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን ለማጉላት ሰፊ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ።

ለዚህም በአብነትነት የሀዋሳ ፍቅር ሐይቅን፣ የጋራንባ ተራራ ባህላዊ ሎጅን፣ የሲዳማ አፊኒ ሶንጎ ባህላዊ የፍትሕ ሥርዓት ማከናወኛ ስፍራን፣ የተፈጥሮ ፍል ውኃ ስፍራዎችንና ፏፏቴዎችን ጠቅሰዋል።


በተለይም የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ልማት የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን አቶ አበበ አንስተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ክልሉን ከ3 ሚሊዮን 280 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች መጎብኘታቸውንና ከዚህም 3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።


ከአዲስ አበባ ሀዋሳን ለመጎብኘት የመጡት አቶ ዘላለም ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት፤ የሀዋሳ ከተማ ዕድገት፣ የኮሪደር ልማቱና የሐይቅ ዳርቻ ማሻሻያው የቱሪስቶችን ቀልብ መሳብ የሚችሉና ከተማዋን ተመራጭ መዳረሻ የሚያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሀዋሳ ከተማን ለእረፍት ጊዜያቸው ዘወትር እንደሚመርጧት የገለጹት ደግሞ ሰላማዊት እሸቱ ናቸው።


ለዚህም የከተማዋ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ የቱሪስት መዳረሻዎች፣ እንዲሁም የሐይቅ ዳርቻ ልማቱ ከተማዋን ይበልጥ ሳቢና ማራኪ እንዳደረጋትም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026