የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል።


በምክር ቤቱ የድጎማ በጀት እና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የ 2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን አድምጧል።

የቋሚ ኮሚቴው ጸሐፊ ኃይሉ ኢፋ ባቀረቡት ሪፖርት የፊስካል ሽግግሮችን በፍትሐዊነት እና በውጤታማነት ለማስፈጸም የሚያግዙ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።

የአቅም ግንባታ፣ የጋራ ገቢዎች ክትትል፣ የጥቅል ድጎማ ቀመር ማሻሻያ ዝግጅት እና የውስን ዓላማ ድጎማዎች ላይ ውጤታማ ስራ መከናወኑን ጠቁመዋል።


በቀጣይም በጠንካራ ክትትል፣ በየጊዜው የአፈጻጸም ግምገማ በማድረግ እና በመደገፍ ወደ ከፍተኛ ተቋማዊ ውጤት ማሸጋገር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የምክር ቤቱ አባላት ክልሎችን ለመደገፍ ያከናወኑት ሥራ አመርቂ ውጤት እና ጠንካራ የሀብት አስተዳደር የታየበት መሆኑን ጠቁመዋል።

ለውጡ ፍትሐዊ ግልጽነት የታከለበት ስርዓት እንዲኖር ማስቻሉን ገልፀው፤ ሀብቶች ስራ ላይ መዋላቸውን መከታተል እንደሚገባ አመላክተዋል።


የድጎማ በጀት እና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሽመልስ አብዲሳ በግልጽነት፣ ሕገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ፍትሐዊ ልማትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ፍትሐዊ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን በማስፋፋት በኩል ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን እና አዳዲስ አሠራሮች መዘርጋታቸውን ገልጸው፥ የነበሩ ክፍተቶችም መቀረፋቸውን ጠቁመዋል።

ክልሎች ከድጎማ ጎን ለጎን የራሳቸውን የልማት አቅም ለማሳደግ መሥራት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም አንስተዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን ጠቁመዋል።

ፍትሐዊ የመሠረተ ልማት ሥርጭትን በማስፋፋት በኩል የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026