የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል ተችሏል- አቶ ሽመልስ አብዲሳ

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።

አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት በ2018 በጀት ዓመት በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማትንና የዜጎችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።

የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ክፍፍል ሥርዓት በጥናትና በተደራጀ ዕቅድ እንዲመራ ከማድረግ ባሻገር ወደ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚተላለፉ ሀብቶች ግልጽና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲከፋፈሉ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።


በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን ገልጸዋል።

ይህም የሚተላለፉ ሀብቶች ላይ ግልጽነትን ለማሳደግና የበይነ መንግሥታት የፊስካል ሽግግር ሥርዓትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አብራርተዋል።

በተጨማሪም የፌዴራል መሠረተ ልማት ስርጭት ፍትሐዊነትን ማስፈን እንዲሁም ልዩ ዓላማ ያላቸው ድጎማዎች በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ ለክልሎች መከፋፈላቸውን ማረጋገጥ የኮሚቴው ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ተግባራት እንደነበሩ አመልክተዋል።

የኢኮኖሚና የማሕበራዊ ዕድገትን ማፋጠንና በክልሎች መካከል ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ የረጅም ጊዜ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸው ማነቆዎችን በመለየትና መረጃዎችን በወቅቱ በማሰባሰብ ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማምጣት ይሰራል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026