🔇Unmute
አዲስ አበባ፣ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት በ2018 በጀት ዓመት በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማትንና የዜጎችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ክፍፍል ሥርዓት በጥናትና በተደራጀ ዕቅድ እንዲመራ ከማድረግ ባሻገር ወደ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚተላለፉ ሀብቶች ግልጽና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲከፋፈሉ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ የሀብት ማከፋፈያ ቀመሮች በአግባቡ መተግበራቸውን በቅርበት መከታተል መቻሉን ገልጸዋል።
ይህም የሚተላለፉ ሀብቶች ላይ ግልጽነትን ለማሳደግና የበይነ መንግሥታት የፊስካል ሽግግር ሥርዓትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አብራርተዋል።
በተጨማሪም የፌዴራል መሠረተ ልማት ስርጭት ፍትሐዊነትን ማስፈን እንዲሁም ልዩ ዓላማ ያላቸው ድጎማዎች በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ ለክልሎች መከፋፈላቸውን ማረጋገጥ የኮሚቴው ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ተግባራት እንደነበሩ አመልክተዋል።
የኢኮኖሚና የማሕበራዊ ዕድገትን ማፋጠንና በክልሎች መካከል ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ የረጅም ጊዜ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸው ማነቆዎችን በመለየትና መረጃዎችን በወቅቱ በማሰባሰብ ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማምጣት ይሰራል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026