🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የቱሪዝም መዳረሻ ልማትና የቅርስ ጥበቃ ስራ ከፍተኛ ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ገለጸ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ቱሪዝም አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር!” በሚል ከቀናት በፊት በሰጡት ማብራሪያ የብዝሃ የኢኮኖሚ አማራጮችን መሰረት በማድረግ በተለይም በቱሪዝም ዘርፍ የተመዘገበውን ዘርፈ ብዙ ስኬት ገልጸዋል።
በተለይም የገበታ ፕሮጀክቶች ግንባታ፣ የከተሞች ኮሪደር ልማትና የቅርሶች እድሳትና ሌሎችም ተግባራት ለዘርፉ እድገትና ማንሰራራት ወሳኝ ስለመሆናቸው አንስተዋል።

ከዚህ አንፃር በአማራ ክልል በቱሪዝም ልማት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትንና የመጡ ለውጦችን በማስመልከት የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ መልካሙ ፀጋየ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በገበታ ለሀገርና ለትውልድ የተከናወኑ አስደናቂ የቱሪዝም ልማት ፕሮጀክቶችን፣ የቅርሶች እዲሳት እንዲሁም በከተሞች ኮሪደር የተከናወኑ ሰፊ ስራዎችን አንስተዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት፣ ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የተሰሩት የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት እና የለጎ ሃይቅ ሪዞርት በጉልህ የሚነሱ ናቸው ብለዋል።
እነዚህ ፕሮጀከቶች ዓለምአቀፍ ደረጃን የጠበቁ፤ በፍጥነትና በጥራት የተገነቡ ዘመን ተሻጋሪ አሻራ ያረፈባቸው ድንቅ ስራዎች መሆናቸውን አንስተዋል።

የፋሲል አብያተ መንግስታትን ጨምሮ ሌሎች ነባር ቅርሶችን በማደስ፣ በመንከባከብና ይበልጥ በማስዋብ የሃብት ምንጭ ከማድርግ ባለፈ በመጠበቅ ከተጋረጠባቸው የህልውና አደጋ መታደግ የተቻለበት እንደሆነም ነው ያነሱት።
በእነዚህና በዘርፉ ልማት በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በክልሉ የቱሪዝም ዘርፍ እድገትና ማንሰራራት እያሳየ መምጣቱን ገልጸዋል።
በዚህም ዓመት የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ቁጥር ማደጉን ጠቅሰው ከ16 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
በዘርፉ የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመው ክልሉ ያለውን እምቅ የቱሪዝም ሃብት የማልማትና ይበልጥ የማስተዋወቅ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለይም የፋሲል አብያተ መንግስታት፣ የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትና ሌሎችም በጎብኚዎች ተመራጨ የጉብኝት መዳረሻዎች እንደነበሩ ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026